Saturday, January 24, 2015

የሬዲዮ ፋና፣ ኢትቪ እና ምርጫ ቦርድ ግንባር በአንድነት ላይ ግርማ ሠይፉ ማሩ

 እነዚህ ተቋማት አንድነት ፓርቲን ለማጥፋት የተደራጁ የጥፋት ተቋሞች ናቸው፡፡ ሰሞኑ ጠዋት በማለዳ፣ በምሳ ሰዓት ይሁን ደክሟችሁ አረፍ ባላችሁበት ምሽት ወሬው ሁሉ አንድነት፣ አንድነት፣ አንድንት ሆኖዋል፡፡ ኢቲቪ የህዝብ አሰተያየት በሚል በማያገባው ገብቶ ሲየስፈልገው ዶክመንተሪ ሰርቶ በአንድነት የውስጥ ጉዳይ ገብቶ የሚፈተፍተውን ምርጫ ቦርድ ሆደ ሰፊነት እየነገረን ይገኛል፡፡ እነዚህ ተቋማት በምንም መመዘኛ በኢትዮጵያችን የመድበለ ፓርቲ ስርዓት እንዲያብብ አይፈልጉም፤ ቢፈልጉም አለቆቻቸው ካስቀመጡላቸው መስመር ወጥተው ይህን ፍላጎታቸውን ማስፈፀም የሚያስችል የሞራል ልዕልና ባላቸው ሰዎች ዙሪያ የተዋቀሩ አይደሉም፡፡ ሁሉም በሚባል ደረጃ ለሆዳቸው እንዳደሩ ተግባራቸው ምስክር ነው፡፡ የሆደ ሰፊነት ትርጉማቸው ከዚህ የሚዘል አይደለም፡፡ ለሆዱ ያደረን ደግሞ ለመርዕ ይገዛል ብሎ መጠርጠር ተገቢ አይደለም፡፡ ሆዳም ሆዳም እንጂ ከህሊናው ጋር ግንኙነት የለውም፡፡
ሬዲዮ ፋና በ1987 ተመሰረትኩ ይበል እንጂ ከጫካ ጀምሮ የኢህአዴግ ልሳን ሆኖ የመጣ የሚዲያ ተቋም ነው፡፡ በኢትዮጵያ ህግ ፓርቲዎች ሬዲዮ ጣቢያ ማቋቋም ክልክል ቢሆንም ገዢው ፓርቲ በግል ተቋም ስም ይህን ተቋም በማቋቋም በፈለገው ጊዜ ካርድ እየመዘዘ አጀንዳ ማሰቀመጫ እና ህዝብን ማወናበጃ ያደርገዋል፡፡ ሲፈልግ ደግሞ ኮንፈረንስ አዘጋጅቶ ውይይት አድርጉ ብሎ የሬዲዮና የቴሌቪዥን ድራማ ይስራል፡፡ ገዢው ፓርቲ ለሚወስዳቸው እርምጃዎች ሁሉ የቅድሚያ ፋና ወጊ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል፡፡ ይህ ሬዲዮ ጣቢያ በምንም መመዘኛ ስልጣን ከኢህአዴግ እጅ እንዲወጣ አይፈልግም፡፡ ይህን ለማድረግ ደግሞ ሌት ተቀን ይሰራል፡፡ አሁንም በተግባር በአንድነት ፓርቲ ላይ እያደረገ ያለው ይህንን ነው፡፡ ምርጫ ሲቃረብ አማራጭ አለን የሚሉ ፓርቲዎችን ከስር ከስር እየተከተለ መሰረተ ቢስ ዜና፣ ዜና ትንተና፣ ሲያስፈልገው ሙሉ ፕሮግራም ሰርቶ ህዝብን ውዥንብር ውሰጥ ይከታል፡፡ ለዚህ ተግባር ደግሞ የሚውሉ በፓርቲዎች ውስጥም ዙምቢዎች አይጠፉም፡፡ ትግሰሰቱ አወሎም እና መሰሎችን የመሰለ ዙምቢዎች ለማግኘት ደግሞ ብዙ ርቀት መሄድ አያሰፈልግም፡፡
ሰሞኑን እንደተከታተላችሁት በአንድነት ውስጥ የአመራር ክፍፍል አለ የሚል ዋነኛ ርዕስ ሆኖ ቀርቦዋል፡፡ በአንድነት ውስጥ ይህ የሚሉት መዓት የሌለ ቢሆንም የአመራር ክፍፍል ቢኖር እንኳን ሬዲዮ ፋና ለአንድነት ጥንካሬ ይስራል ብሎ ማመን አይቻልም፡፡ ይህ ማለት ኢህአዴግ አንድነትን ለማጠናከር በጀት በጅቶ አንድነትን አጠናክሮ ስልጣኑን ለመልቀቅ ተዘጋጅቶዋል እንደ ማለት ነው፡፡ እኛ ከኢህአዴግ የምንጠብቀው እራሱን ከተቸነከረበት ችንካራ ለማውጣት ተግቶ መስራት፤ እኛ ደግሞ በሰላም ለመደራጀት እንድንችል መንግሰታዊ መዋቅሩን በህግና በህግ ብቻ እንዲሰሩ ማድረግ ነው፡፡ ሬዲዮ ፋና ለህገወጥነቱ ዋጋ የሚከፍልበት ጊዜ ይራቅ እንጂ እንደሚኖር ጥርጥር የለኝም፡፡ አንድነትን እና አመራሩን ህገወጥ ብሎ ለመፈረጅ የገዙትን መኪና እና ፎቅ ያለመረጃ በሚዲያ ከሚያቀርብ ግን በዚሁ በያሰዘው እጁ የአለቆቹን ህንፃ ቆጥሮ ከየት አመጣችሁት? ቢልልን ባይገባውም ክብር እንሰጠው ነበር፡፡ በነገራችን ላይ ሬዲዮ ፋና ይህንን ፎቅ ከየት አመጣው?
ኢቲቪ የሚባል የሚዲያ ተቋም የስም ለውጥ አድርጌያለሁ ቢልም ግብሩን መቀየር ግን የተሳነው ተቋም ሆኗል፡፡ አንድነት ፓርቲ የተለያዩ መግለጫዎች ሲሰጥም ሆነ በአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ተገኝቶ ፊልም ከመቅረፅ የዘለለ አንድም የረባ የሚዲያ ስራ አይሰራም፡፡ በገዢው ፓርቲ ሹሞች እጅ የወደቀ በመሆኑ ዘወትር አማራጭ አለን የምንል ፓርቲዎችን ችግር ብቻ ሲዘግብ ይኖራል፡፡ የዛሬ አምስት ዓመት አጥር ላይ ሆኖ አንድነቶች ተደባደቡ ሲል የነበረው ኢቲቪ፤ ምንም ፎርማት ሳይቀይር አንድነቶች ተሰነጠቁ ለማለት ዛሬም አይቸገርም፡፡ ኢቲቪ አንድነት ተሰነጠቀ ብሎ ከመዘገብ ባለፈ ስለ ገዢው ፓርቲ ልማታዊነት ዘወትር ኢህአዴግ ስለ አመጣው ልማት የደም ስራቸው እስኪገተር የሚያላዝኑ ጋዜጠኞች ማምረትም የተቸገረ አይመስለም፡፡ ህዝቡ አንድነት ፓርቲን እንደ አማራጭ እንዳይመለከት የገዢውን ፓርቲ ሴራ በህዝብ ዓይንና ጆሮ እንዲደርስ እያደረገ ነው፡፡ ኢቲቪ የሬዲዮ ፋና ጋር ባለው ልዩ ግንኙነት ሬዲዮ ፋና የሰራውን ፕሮግራም ተቀብሎ ያስተጋባል፡፡ ይህን ፕሮግራም ምን አልባትም ኢቲቪ ከሬዲዮ ፋና በግዢ ይሆናል ያገኘው፡፡ ይህን የምልበት ምክንያትም በመንግሰት በጀት የሚተዳደረው ኢቲቪ ለግል ተብዬው ሬዲዮ ፋና ገንዘብ ማቀበያ ዘዴም ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ስለ አለኝ ነው፡፡ ይህ ካልሆነም ሬዲዮ ፋና በነፃም ቢሆን ለኢቲቪ ሰጥቶ አንድነት ለማፍረስ የተያዘውን እቅድ መተግበር ትልቅ ግብና ሰኬት ነው፡፡ እንደ ገዢው ፓርቲ ልሳን አድርገን ስንወስደው ይህ በጣም ቀላሉ የደባ ሰራ ነው፡፡ በነገራችን ላይ የኢህአዴግ አመራሮች አገር ጥለው ሲጠፉ፣ የምክር ቤት አባላት የነበሩ በወጡበት ተሰውረው ግንባሩን ሲያጋልጡ ለምን ኢህአዴግ ተሰነጠቀ ብሎ አይዘግብም፡፡ ትዕግሰቱ አወሉ በአንድነት ፓርቲ ውስጥ የጅማዋ የምክር ቤት አባል ያላትን ያህል ቦታ እንደሌለው ኢቲቪ ሳያውቅ ቀርቶ ነው ያልዘገበው ብለን ልንወስድ አንችልም፡፡ ዋናው ነገር ኢቲቪ ሚናው አንድነትን የማዳከም ብሎም የማፍረስ ዘመቻ ሰለሆነ ብቻ ነው፡፡
ምርጫ ቦርድ ሰሞኑን በግለጫ እንዲዋረድ አደረግነው እንጂ የዘወትር ምግባሩም አንቱ የሚያስብለው እንዳልሆነ ሁሉም ያውቃል፡፡ አንድም ቀን ጠቅላላ ጉባዔ አካሂደው የማያውቁ፤ የፓርቲዎቹ  አመራሮች እነ ማን እንደሆኑ የማይታወቁ፣ የፓርቲ ማህተምና ሰርተፊኬት ይዘው ከተማውን ያጣበቡ ፓርቲዎች በብዛት ባሉበት ሀገር በሰርዓት ለመመራት ወሰኖ የሚንቀሳቀስ ፓርቲን እየተከታተሉ ችግር መፍጠር የተቋሙን ነውረኝነት የሚያሳይ ነው፡፡ ፓርቲዎች ችግራቸውን መፍታት ያለባች በውስጥ ደንባቸው መሆኑ እየታወቀ በሚዲያ እየወጡ ፓርቲዎችን ማጠልሸት ግብ አደርጎ አስቀምጦ፤ ለመድበለ ፓርቲ ስርዓት እሰራለሁ ማለት ተገቢ አይደለም፡፡ ይህንን ተግባር እየፈፀሙ ያሉ የምርጫ ቦርድ ሀላፊዎች የታሪክ ተጠያቂነት እንዳለባቸው የተገነዘቡ አይመስለኝም፡፡ በአንድነት ውስጥ አንድም የአመራር ክፍፍል ሳይኖር የአመራር ክፍፍል አለ ብሎ በሚዲያ ቀርቦ ማውራት፤ ሚዲያውም እሰኪ ማን ነው አመራር? በምን ደረጃ? ብሎ እንዳይጠይቅ የተደረገበት ምክንያት ዘመቻው በቅንጅት የሚተገበር ከገዢው ፓርቲ የተሰጠ ተልዕኮ መሆኑ ጉልዕ ምስክር ነው፡፡ ሬዲዮ ፋና እየሰራ ያለው የኢህአዴግ (የአባቱን) ገዢነት እድሜ ለማራዘም ነው፡፡ እነርሱ በወንጀል እንጂ በታሪክ ፊት አይቆሙም፡፡ ምርጫ ቦርድ ግን ሁለቱም የሚቀርለት አይደለም፡፡
ይህ ሁሉ የሚደረገው ዜጎች በፖለቲካ ጉዳይ አማራጭ እንዳይኖራች ማድረግ እና ገዢውን ፓርቲ አውራ ፓርቲ አድርጎ ለማቆየት የተወሰደደው አማራጭ ገዢውን ፓርቲ ከማጠናከር ይልቅ አማራጮችን ማደከም እንደ ስልት በመያዙ ነው፡፡ ይህ ሰልት ደግሞ በሌላ ግንባር አማራጭ በሚፈልገው ወጣት ላይ በግልፅ ተከፍቶ ታገኙታላችሁ፡፡ በዚህኛው ግንባር አማራጭ ሞልቷል፡፡ እግር ኳስን በሬዲዮ ይሁን በቴሌቪዥን መመልክት፣ ሙዚቃ፣ መጠጥ፣ ጫት፣ ሲጋራና አሽሽ የመሳሰሉት ለወጣቶች የቀረቡ አማራጭ መፋዘዣ እና ማደንዘዣ ናቸው፡፡ ለሀገሬ ያገባኛል ብሎ ግን በፖለቲካ ፓርቲ ወይም በማህበራዊ ሚዲያ መጠቀም፣ ለሰላምና ለለውጥ የሚጠቅም ስራ መስራት ግን ያስወነጅላል፡፡ ያለ ስም ስም ያሰጣል፡፡
ይህን በተመለከተ አንድ ወጣት ጓደኛዬ ስልክ ደውዬለት የትነህ?  ምን እያደረክ ነው? የሚል ተከታታይ ጥያቄ ሳቀርብለት የሰጠኝ መልስ መንግሰታችን በዚህ በኩል ልቅ እንደሆነ ማሳያ ይሆናል፡፡ መንግሰታችን የሚወደውን ቢራ እየጠጣሁ ነው አለኝ፡፡ አስከትሎም ቢራ ጠጥተህ ሰክረህ ብትጮሆ፣ ወይም ኳስ አፍቃሪ ነኝ ብለህ ማንቼና አርሴ እያልክ ብትሰበሰብ ማንም ምንም አይልህም፡፡ ነገር ግን የዚህ ሀገር ጉዳይ ያገባኛል ብለህ ላይብረሪ ሄደህ አንብበህ የተሰማህን ለህዝብ ለማድረስ ከፃፍክ ግን ቤትህ ወህኒ ይሆናል አለኝ፡፡ እኔም እንደምታውቀው ያገባኛል ብዬ የአንድነት ፓርቲ አባል ሆኜ ፖለቲካ ውስጥ ስሳተፍ ድርጅቴን ለማፍረስ ምርጫ ቦርድ በሚባል ተቋም ውስጥ የመሸጉ ጉግ ማንጉጎች የሚሰሩትን እያየህ ነው አለኝ፡፡ በእኔ እምነትም ይህ የምርጫ ቦርድ አጎራ ዘለል ተግባር  ሚዛን የጠፋለት ነውረኛ ተግባር እንደሆነ አሁን ግልፅ እየሆነ የመጣ ይመስለኛል፡፡ ሁላችሁም እንደምታውቁት ይህ ወጣት የትግል አጋር በግልፅ እንዳሰቀመጠው ወጣቱ በሀሽሽ ቢናውዝ፣ ሰክሮ ቢጨፍር፣ እህቶቻችን እርቃናቸውን ውጪ ሲሄዱ ቢያድሩ፣ ጫት፣ ሺሻ ሲጀነጀኑ ውለው ቢያድሩ መንግሰት ተብዬው ከቁም ነገር የሚቆጥረው ነገር አይደለም፡፡ ነገር ግን ወጣቶች በምርጫ በመራጭነትና በታዛቢነት ከፍ ሲል ደግሞ በዕጩነት ለመሳተፍ ፍላጎት ካሳዩ ግን የማይሸርበው ሴራ የለም፡፡
በቅርቡ የምርጫ ቦርድ እና ሚዲያ በአንድነት ፓርቲ ላይ የከፈቱት ዘመቻ ዋና መልዕክት ወጣቱ አማራጭ ስለሌለ ለምርጫ አትመዝገብ የሚል ነው፡፡ ይህን አማራጭ የሚባል የሌለውን ምርጫ ከምትከታተል አርሴና ማንቼ እያልክ ተዝናና፣ ኤፍ.ኤም ሬዲዮኖች የሚለቁልህን ሙዚቃና የስልክ ጥያቄና መልስ፣ ከአውድ ዓመት ጋር ተያይዞ ያለን ሽልማት ላይ ተራኮት፣ ሲመች ደግሞ ማምሻውን ድራፍታ ቢራ እየኮሞከምክ ዓለምህን ቅጭ እየተባለ ነው፡፡ አማራጭ ያለበት ምርጫ ስልጣኑን እንደሚያሳጣው የተረዳው ገዢው ፓርቲ ምርጫ ቦርድን ከለላ አድርጎ ፍልሚያ ከፍቶዋል፡፡ ከህዝብ በተሰበሰበ ገንዘብ ደሞዛቸውን የሚበሉ የቦርድ ሰራተኞችና ሹሞኞች በማን አለብኝነት የእብድ ገላጋይ መስለው ድንጋይ እያቀበሉ የአንድነትን መንፈስ ለመሰበር ላይ ታች እያሉ ነው፡፡ ይህን ለማሳካት ከምንጊዜውም በላይ ተግተው በስራ ላይ ናቸው፡፡ የሰንበት ቀን አይበግራቸውም፡፡ ኃላፊ ተብዬዎች ነውር የሚባል ነገር አጥተው ደብዳቤዎች ባልተፃፉበት ቀን ወጪ እንዲደረጉ በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ በመንግስት ቢሮና ሀብት ከፓርቲ አኮረፍን ያሉ ግለሰቦቸን በፓርቲ ላይ ከህግ ውጭ ያደራጃሉ፡፡ ለመድበለ ፓርቲ ስርዓት ማበብ የመስረት ድንጋይ ያስቀምጣሉ ተብለው የሚጠበቁ ሰዎች መሰረቱን ንደው ለአውራ ፓርቲ ግንባታ እራሳቸውን አዋርደው ይስራሉ፡፡ እራሳቸውን ያዋረዱ ሰዎችን ደግሞ በምን መመዘኛ ለክብር እንደምናጫቸው እየተቸገርን ነው፡፡ በእነዚህ ሰዎች የሚመራ ተቋም ደግሞ ክብር እንዴት ሊያገኝ ይችላል፡፡ እጅግ ጥቂት የሚባሉ ከህሊናቸው ያሉ ካሉ ግን ሳይረፍድ የመድበለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ መሰረት እንዲጥል በተቋቋመ ተቋም ውስጥ እየተሰራ ያለውን ደባና ህገወጥ ተግባር ሊያጋልጡ ይገባል፡፡ ጥሪው ሀገራው ጥሪ ነው፡፡ በምንም ዓይነት ይህ ተቋም በመድበለ ፓርቲ ስርዓት ግንባታ ላይ ሽፍጥ የሚሰራበት መሆን የለበትም፡፡ ሽፍጠኞችም በህዝብ ዳኝነት የሚያገኙበት ጊዜ እሩቅ አይሆንም፡፡
ለማነኛውም ኢትዮጵያ ሀገራችን ነች በምንም ሁኔታ ቢሆን ለጊዜው ህገወጦች ሊያይሉ ይቸላሉ ህጋዊ መስመር ላይ ያሉ የተሸነፉ ይመስላሉ እውነቱ ግን የተለየ ነው፡፡ ለእውነት የቆሙ ከመርዓቸው ጋር የሆኑ ሁሉ ያሸንፋሉ፡፡ ለማሸነፍ ሁሌም ከመርዕ ጋር መሆን ጠቃሚ ነው፡፡ መርዕ ሲባል ግን ለሆድና ለግል ዝና መቆም አይደለም፡፡ መርዕ ሲባል ከግል ጥቅም እና የግል ፍላጎት አለመገዛት ነው፡፡ ፈረንጆቹ እንደሚሉት ለግል ፍላጎት ግዴለሽ መሆን ማለት ነው፡፡ አንድነት አባላት አሁን የሚፈልጉት ከግል ፍላጎታቸው የነጹ እና ለውጤት የሚተጉ አመራሮች ነው፡፡ ለውጥ ግን የግድ ነው፡፡ አንድነት ይምራው ወይስ ሌላ ይህ የታሪክ ጥሪ ነው፡፡

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

Friday, January 16, 2015

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በ573/200 አንቀፅ 21/1 መሰረት የአመራሮች ዝርዝር



የአንድነት ፓርቲ አመራር ክፍፍል አለበት እያሉ የምርጫ ቦርድ ኃለፊዎች በተደጋጋሚ እየፈጠሩት ባለው ውዥንብር የሚያጠራ ከሆነ ይህንን መረጃ ለህዝብ ይፋ ማድረግ ተገቢ መሰለኝ፡፡ በዚህ መሰረት ደግሞ አቶ ትዕግሰቱ አወሉ በኢ/ር ግዛቸው ሸፈራው የመጨረሻው ካቢኔ ውስጥ የተካተተ ሲሆን ይህ አመራር ለአንድ ወርም ስለአልቆየ ወደ ምርጫ ቦርድ አልገባም፡፡ ትዕግሰቱ አወሉ ኢ/ር ግዛቸው እንዲወርድ ሌት ተቀን ሲሰራ የነበረ ሲሆን አቶ የማነአብ አሰፋ እና አቶ ትዕግሰቱ አወሎ በበላይ ካቢኔ እንደማይገቡ ሲያውቁ የተነሳ ሽፍጥ ስራ ነው፡፡ ለማነኛውም እዚህ አመራር ውስጥ ምርጫ ቦርድ በስሙ አመራር እያለ ደብዳቤ የፃፈለት አቶ አየለ ሰሜነህ የሚባል ሰው የለም፡፡ የምርጫ ቦርድ፣ የሬዲዮ ፋና እና የኢቲቪ የአንድነት አመራር ተከፋፈለ አንባ ይፍረደን፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
የብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ
በ573/200 አንቀፅ 21/1 መሰረት የአመራሮች ዝርዝር

ሙሉ ስም
ሙሉ ስም
ሙሉ ስም
ሙሉ ስም
ኃላፊነት
1
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ
ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው
ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው
አቶ በላይ ፍቃዱ በረዳ
ፕሬዝዳንት/ሊቀመንበር
2

አቶ ተክሌ በቀለ ጀመረ
አተ ዘለቀ ረዲ
አቶ ተክሌ በቀለ ጀመረ
ተ/ም/ፕሬዝደንት
3
የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ ማሩ
አቶ በላይ ፍቃዱ በረዳ
አቶ ብሩ ቢርመጂ ጪቋላ
የተከበሩ አቶ ግርማ ሠይፉ
ም/ፕሬዝዳንት
4
አቶ አሰራት ጣሴ
አቶ ሰዩም መንገሻ ወ/ሰማያት
አቶ ሰዩም መንገሻ ወ/ሰማያት
አቶ ስዩም መንንገሻ ወ/ሰማያት
ዋና ፀኃፊ
5
አቶ ዘለቀ ረዲ/ሰዩም መንገሻ
አቶ ዳንኤል ተፈራ ጀምበሬ
አቶ ዘካሪያስ የማነ ብርሃን ኃ/ማሪያም
አቶ ዘካሪያስ የማነ ብርሃን ኃ/ማሪያም
የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ
6
ዶ/ር ኃይሉ አርሃያ/ዳንኤል
አቶ ሀብታሙ አያሌው
-
አቶ አስራት አብርሃም 
የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
7
አቶ ተመስገን ዘውዴ
አቶ ዘለቀ ረዲ
አቶ ትዕግሰቱ አወሉ
አቶ ዳንኤል ተፈራ ጀምበሬ
የውጭ ግንኙነት ኃላፊ
8
አቶ ሙላት ጣሳው
አቶ ሰለሞን ሰዩም
አቶ እንግዳ ወልደፃድቅ መንገሻ
አቶ ብሩ ቢርመጂ ጪቋላ
የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ
9
አቶ ወንደሰን ፀጋዬ
አቶ ትንሣዔ ደነቀው
አቶ ትንሣዔ ደነቀው
አቶ ደረጀ ኃይሉ ወልደየስ
የኤኮኖሚ ጉዳይ ኃላፊ
10
አቶ ሽመልስ ሀብቴ
አቶ አለነ ማፀንቱ አዳል
አቶ አለነ ማፀንቱ አዳል
አቶ አለነ ማፀንቱ አዳል
የማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ
11

አቶ የማነአብ አሰፋ
አቶ የማነአብ አሰፋ
አቶ እንግዳ ወልደፃድቅ መንገሻ
የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ
12

ወ/ሮ እልፍነሽ  ከበደ
ወ/ሮ እልፍነሽ
ወ/ሮ እመቤት ኃይሌ ወ/መድህን
የሴቶች ጉዳይ ኃላፊ
13
አቶ ደምሴ መንግስቱ ጃጃት
ወ/ሮ የትናዬት ቱጂ
አቶ ደምሴ መንግስቱ ጃጃት
አቶ ደምሴ መንግሰቱ ጃጃት
የህግና ሰ/መ/ጉ ኃላፊ
14

አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን ኃ/ማሪያም
-
አቶ ነገሰ ተፈረደኝ ጥላዬ
የአ/አ ምክርቤት ስብሳቢ
15
አቶ ተክሌ በቀለ ጀመረ
አቶ አሰቻለው ከተማ
አቶ ነገስ ተፈረደኝ ጥላዬ
አቶ አለማየሁ በቀለ
የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ




Wednesday, January 14, 2015

ግልፅ ደብዳቤ
ለክቡር ፕሮፌሰር መርጊያ በቃና
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስብሳቢ
ከግርማ ሠይፉ ማሩ (በግል)
ጉዳዩ፤ በሚዲያ ቀርበው አንድነት ፓርቲትን በተመለከተ የሰጡትን የቦርድ ውሳኔ ይመለከታል
ቦርዱ ሰጠ የተባለውን ውሳኔው ከመግለጫው እንደተረዳሁት የውስጥ ችግራቸውን ፈተው በጋራ ጉባዔ እንዲጠሩና የሚመራቸውን ፕሬዝዳንት ይምረጡ የሚል ነው፡፡ ቦርዱ በግልፅ ፕሬዝዳንት ይምረጡ ባይልም ታህሳስ 28 ቀን 2007 ዓ.ም በቁጥር አ/573/ፓአ/405 በተፃፈልን ደብዳቤ ይዘት ስንረዳ የቦርዱ ጥያቄ በዋነኝነት የሚያጠነጥነው በፕሬዝዳንት ምርጫ ላይ በመሆኑ ነው ይህን ግምት ለመውሰድ የተገደድኩት፡፡ ከዚህ በመነሳት በአንድነትፓርቲ በአባላት መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት የሚፈታበት ህገ ደንብ አለው፡፡ ከዚህ ውጭ ቦርዱ በፓርቲ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዲገባ በየትኛው ህግና ደንብ ወይም መመሪያ እንደተሰጠው መረዳት ተቸግሪያለሁ፡፡ የቦርዱ ስብሳቢ ዘወትር እንደሚሉት በቅንነትና በሆደ ሰፊነት ከሆነ ግን በምንም መመዘኛ እርሶ የሚመሩት ቦርድም ሆነ እርሶ በግል ለፓርቲያችን እድገት ቅን እንደማታሰቡ እሰከ አሁን ባደረግናቸው ውይይቶችና ቦርዱ በሚፈፅማቸው ድርጊቶ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ አሁንም በህግ አመልካ ከፓርቲያችን የውስጥ ጉዳይ እጃችሁን እንድታነሱልን እጠይቃለሁ፡፡
ሌላው የቦርዱ ውሳኔ ከሚዲያ እንደሰማሁት በጋራ ጉባዔ ጥሩ የሚለው ነው፡፡ ክብር ሰብሳቢ ዘወትር በውይይታችን የሚያነሱልን የህግ አማካሪዎች በበቂ እንዳላችሁ፣ የፅ/ቤቱ ኃላፊም የህግ ባለሞያ እንደሆኖ የምትሰሩትም በህግና በህግ ብቻ እንደሆነ ነው፡ ፓርቲያችንንም የውስጥ ደንቡን ጨምሮ ሌሎች ህጎችን እንዲያከብር ዘወትር ይመክሩናል፡፡ ሀቁ አንድም ቀን ከህግ ውጭ ሰርተን አለማወቃችን ሲሆን ይልቁንም ቦርድ የሚላቸውን ጉዳዮች ከመስመር ወጥተን ለማስተናገድ መሞከራችን ነው፡፡

ይህ ሁሉ ባለበት ሁኔታ በጋራ ጉባዔ ጥሩ ሲባል የአንድነት ፓርቲ መተዳደሪያ ደንብ የጉባዔ አጠራር እንዴት እንደሆነ ካለማወቅ ነው የሚል እምነት የለንኝም፡፡ ይልቁን አንድነትን ወደ ሌላ ህገወጥ ተግባር በመክተት ችግሮችን ለማወሳሰብ በፅ/ቤታችሁ በኩል እየተሰራ ያለውን ህገ ወጥ ግለሰቦችን የማደራጀት ደባ እኛ በምንፈፅመው ስህተት ለማጠናከር ነው የሚል ፅኑ እምነት አለኝ፡፡ ክቡር ሰብሳቢ የአንድነት ፓርቲ ደንብ የጠቅላላ ጉባዔ የመጥራት ስልጣን የሰጣቸው ህጋዊ አካላት እና አጠራሩ፤
1.  የብሔራዊ ምክር ቤት፤
2.  የኦዲትና ኢንስፔክሽን አባላት ጉባዔ በማንኛውም ምክንያት ጉባዔ እንዲጠራ ከፈለጉ የጠቅላላ ጉባዔ አባላትን አንድ ሶስተኛ አሰፈርመው ሲያቀርቡለት በዚሁ መሰረት ብሔራዊ ምክር ቤቱን ሲያዝ፤ ወይም፤
3.  ብሔራዊ ምክር ቤቱ ትዕዛዙን ካልፈፀመ ኦዲትና ኢንስፔክሽን በቀጥታ ጉባዔ እንዲጠራ
 በማድረግ ነው፡፡
ከዚህ ውጭ የፓርቲው ፕሬዝዳንት እንደ ፓርቲ ከፍተኛ መሪ ወይም የፓርቲው ስራ አሰረፃሚ ኮሚቴ እንደ አካል የብሔራዊ ምክር ቤት የመጥራት ስልጣን የላቸውም፡፡ ከዚህ አንፃር ሲመዘን ሁለት ጠቅላላ ጉባዔ ተካሄደ ብለው በሚዲያ የሰጡት መግለጫ አግባብነት የሌለው ነው፡፡ ይልቁን በርሶ ደረጃ በኃላፊነት ያለ ግለሰብ በሚዲያ ቀርቦ “መሪዎች ክሊክ እየሰበሰቡ የሚያካሂዱት ጉባዔ” በማለት በመረጃ ያልተደገፈ ያልተገባ ቃላት ተጠቅሞ መግለጫ መስጠት ከባድ ስህተት መሆኑን እና በህግ የሚያስጠይቅ እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ 
ከዚህ ውጭ በጋራ ጠቅላላ ጉባዔ ሊጠራ የሚችልበት ሁኔታ ካለ ቦርዱ ህግ ጠቅሶ ቢያስረዳን ለመማር ዝግጁ ነኝ፡፡ ይህ በማይሆንበት ሁኔታ የፓርቲው መልካም ስምና ዝና የማይመጥን መግለጫ በሚዲያ እየቀረቡ መስጠት ምርጫ ቦርዱ የአንድነት ፓርቲ በቆራጥነት ምርጫ ለመሳተፍ መወሰኑን ተከትሎ በገለልተኝነት ለማገልገል አለመዘጋጀቱን ነው፡፡ አሁን እየተደረገ ባለው ህገ ወጥ ተግባር ምክንያት ፓርቲያችን መራጩ ለምርጫ በንቃት እንዲሳተፍ ለመቀስቀስ ፓርቲያችን ያለውን እቅድ በከፍተኛ ደረጃ እያስተጓጓለ ሲሆን፣ በፓርቲው ዕጩ አመላመል ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረብን መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ ጭምር እንዲያውቅ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ ደግሞ በገለልተኝነት እንዲያገለግል የሚጠበቅበት የምርጫ ቦርድ ለገዢው ፓርቲ ግልፅ ወገንተኝነት በማሳየት የህግ ጥሰት እየፈፀመ መሆኑን ያጋልጣል፡፡
በመጨረሻም ቅሬታ አለን የሚሉት አባላት በፅ/ቤቱ ቀጥተኛ ድጋፍ የሚደረግላቸው እና ዝርዝራች በቦርድ ፅ/ቤት የሚታወቅ ሲሆን አንድነት በጠራው ጉባዔ ላይ እንዲሳተፉ ጥሪ የደረሳቸው ስለመሆኑ፤ ነገር ግን በጉባዔው ተገኝተው እንደማይሳተፉ፤ የማይሳተፉበትም ምክንያት በድምፅ ብልጫ አንደሚሸነፉ ስለሚያውቁ መሆኑን ፤ ወኪል ነን ያሉት በሚዲያ ቀርበው የሰጡት መግለጫ በእጄ ይገኛል፡፡ ቦርዱ ይህን የግለሰቦች ጉዳይ ይዞ ባሰለፈው ህገወጥ ውሳኔ ፓርቲያችን ከምርጫ እንዲወጣና ገዢው ፓርቲ ያለምንም ተቀናቃኝ እንዲሮጥ እየፈቀደ ነው፡፡ ቦርዱ ይህንን ስህተት አርሞ ፓርቲያችን ካቀረባቸው አማራጭ ምልክቶች አንዱን ወሰኖ በአስቸኳይ እንዲያሳውቀን፤ ፓርቲያቸንን የሚመራልንን ሰው መምረጥ ደግሞ የአንድነት አባላት ብቻ መሆኑን ተረድቶ በአዋጅ ቁጥር 573/2000 አንቀፅ 16 መሰረት የፓርቲያችንን ነፃነት እንዲያከብር በማክበር እጥይቆታለሁ፡፡


                            

Sunday, January 11, 2015


የአንድነትን ፓርቲና የምርጫ ቦርድ
ደብዳቤ ልውውጦች ዝርዝር ሁኔታ በማሰረጃ የተመሰረተ
ታህሳስ 19-20፡
አንድነት ፓርቲ ታህሳስ 19-20/2006 ዓ.ም ልዩ ጠቅላላ ጉባዔ አካሄድ፡፡ ይህ ጠቅላላ ጉባዔ ልዩ የተባለበት ምክንያት የአንድነት አምስት ዓመት ስትራቴክ ዕቅድ ላይ በተቀመጠው መሰረት ፓርቲ ከ2007 ዓ.ም ምርጫ ቀደም ብሎ የአመራር ሽግሽግ በማድረግ ፓርቲውን በአዲሰ አመራር ወደ ምርጫ ይዞ ለመግባት በተቀመጠ ግብ መሰረት ነው፡፡ በዚህ ጠቅላላ ጉባዔ ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው የፓርቲው ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጠዋል፡፡ ይህ ጠቅላላ ጉበዔውም የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፎዋል ከዚህ ውስጥ መሰረታዊ ሊባል የሚችለው ጉባዔው በሌለበት ወቅት ፕሬዝዳንቱን ማንሳት የሚያስችል ስልጣን ለብሔራዊ ምክር ቤቱ መስጠቱ ሲሆን ሌሎችም ለምሳሌ የወጣቶች፣ የሴቶች ጉዳይ ኃላፊዎች በስራ አስፈፃሚ ውስጥ እንዲካተቱ ያደረገ ሲሆን የተቀደሚ ፕሬዝዳንት ቦታም እንዲኖረው አድርጎዋል፡፡
አንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባዔውን ባካሄደ በሶስት ወር ጊዜ ውስጥ አመራሩ በሚጠበቅበት ፍጥነት አልሄደም በሚል አለመስማማት የተፈጠረ ሲሆን በአጋጣሚ አንድነት ከመኢህአድ ጋር የሚያደርገው ውህደት ጉዳይ ውይይት በመጀመሩና ለመጠናቀቅ አፋፍ ላይ የደረሰ ሲሆን ይህንንም አጋጣሚ በመጠቀም የውህዱን ፓርቲ የሚመራ የአንድነት ተወካይ ዕጩ ፕሬዝዳንት በብሔራዊ ምክር ቤት ተሰይሞ ውሕደት ይጠናቀቃል ሲባል ውህደቱ እንደማይቻል በምርጫ ቦርድ በኩል ይፋ ተደረገ፡፡ ኢ/ር ግዛቸው ሸፈራው በዚህ አጋጣሚ ተጠቅመው ለወጣት አመራር ቦታ ይለቃሉ ሲባል ይህን ከማድረግ ይልቅ ለውህደት በሚጠራው ጉባዔ በዕጩነት ለመሳተፍ ዝግጁ መሆናቸውን ይፋ አደረጉ፡፡
ሐምሌ 14-30፡
በኢንጅነር ግዛቸው የሚመራው ስራ አስፈፃሚ በታህሳስ 19-20 የተካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ ሪፖርት ገቢ ያደረገው 7 ወር ዘግይቶ ሐምሌ 14 ቀን 2006 ዓ.ም ነበር፡፡ ብዙ ሰዎች ይህ ሪፖርት እንዲዘገይ የተደረገው በአዲሱ አመራር ስለሚመስላቸው ነው ይህን ነጥብ መግለፅ የፈለኩት፡፡ ይህን ሪፖርት መሰረት አድርጎ ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 25 ቀን ዘጠኝ ነጥቦችን አንስቶ ማብራሪያ እንዲሰጠው ጠይቆዋል እነዚህም፤
  1. በጉባኤው ዕለት በቀረበው ሪፖርት የገቡት አላሰፈላጊ ቃላት እንዲወጡ፤
  2. የፓርቲው ባንዲራ እንዲቀርብ፤
  3. ፓርቲው አሻሽሎ ባቀረበው አንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 2 ሰር የተዘረዘረው ሃሳብ ግልፅ አለመሆኑ፤
  4. የጉባዔተኛው ቁጥር አለመገለፁ፤
  5. የፕሬዝዳንቱን በብሔራዊ ምክር ቤት መመረጥ ከህግ አንፃር ያለው ጉዳይ በሚመለከት፤
  6. የፓርቲው የገቢ ምንጭ በአዋጅ ቁጥር 573/2000 መሰረት ያለመቀመጡ፤
  7. የፓርቲ መፍረስ በተመለከተ በአዋጅ ቁጥር 573/2000 መሰረት ያለመቀመጡ
  8. የፓርቲው አባልነት በውርስ እንደማይተላለፍ አለመገለፁ፤ እና
  9. ፓርቲው ያቀረባቸው የፓርቲ አካላት ውስጥ የሚሳተፉ አባላት አድራሻና በኃላፊነት ለመስራ የተሰማሙበት ሰነድ ያለመቅረቡ፤
የሚሉት ናቸው፡፡ ለእነዚህ ለቀረቡት ጥያቄዎች ሐምሌ 30 ቀን  18 ገፅ ያለው ማብራሪያ ተሰጧዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ የመኢህአድና የአንድነት ውህደት አሰመልክቶ ከምርጫ ቦርድ ጋር በሚደረግ ውይይት በአንድነት በኩል ምንም ችግር እንደሌለ ነገር ግን ቦርዱ ሲሰበሰብ ውሰኔ እንደሚሰጥ በተደጋጋሚ ሲነገር ቆይቶ የመኢህአድ ጠቅላላ ጉባዔ ኮረም ሳይሞላ የተካሄደ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም በሚል ሰበብ ውህደቱ እንደማይሳካ በምርጫ ቦርድ ተገለጠ፡፡ ይህንንም ተከትሎ የአንድነት ስራ አሰፈፃሚ ኮሚቴ አባላት የነበሩ አምሰት ከፍተኛ አመራሮች በሰራ አሰረፃሚነት ላለማገልገል መወሰናቸውን ገልፀው መልቀቂያ ደብደቤ አሰገቡ፡፡ ኢንጂነር ግዛቸውም በምትካቸው ሌሎች አመራሮቸን በመሰየም ስራቸውን ለመቀጠል ሞከሩ፡፡
ጥቅምት 3፤
ኢንጂነር ግዛቸው ሸፈራው የብሔራዊ ምክር ቤቱን ጠርተው በጥቅምት ሁለት ካቢኔያቸውን ማሰናበታቸውን በመግለፅ ከውስጥና ከውጭ በደረሰባቸው ጫና ለፓርቲው እልውና ሲሉ ጠቅላላ ጉባዔ የሰጣቸውን ኃላፊነታቸውን ለመልቀቅ እንደወሰኑ ለምክር ቤት አቀረቡ፡፡ ምክር ቤቱም ኃላፊነት ለመልቀቅ መወሰናቸው ተቀብሎ ፓርቲው አመራር በቀጣይ እንዴት መሆን አለበት በሚል ባደረገው ከፍተኛ ውይይት ፓርቲው ለአንድ ቀንም ያለ አመራር ማድር እንደማያስፈልግ ታምኖበት ከዚህ በፊት የመኢህአድና አንድነት ውሕደት አስመልክቶ ለዕጩነት ሲንቀሳቀሱ የነበሩትን ጨምሮ ሌሎች ተጨማሪ ዕጩዎች በፈቃደኝነት ቀርበው ውድድር ተደርጎ በሚስጥር ደምፅ አስጣጥ በተደረገ ምርጫ አቶ በላይ ፍቃዱን በፕሬዝዳንትነት ሰየመ፡፡ በሳምንቱ ጥቅምት 10 ደግሞ የስራ አስፈፃሚ ኮሚቴውን ሰይሞ ስራውን በይፋ ጀመረ፡፡
ጥቅምት 19-21፤ የምርጫ ቦርድ ፅ/ቤት ምክትል ኃለፊ ጥቅምት 19 በተፃፈ ደብዳቤ አንድነት ፓርቲ ያደረገው የፕሬዝዳንት ምርጫ በታሕሳስ 19-20 በተደረገው ጉባዔ የተሻሻላው ደንብ በቦርዱ ባለፀደቀበት ሁኔታ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም የሚል ስሜት ያለው ደብዳቤ ሲፃፍልን፣ በዚህ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ጥቅምት 20 የቦርዱ ፅ/ቤት ኃላፊ ጋር ለመነጋገር የፓርቲ ወኪሎች ስንሄድ የቦርዱን ጥቅምት 19 ያደረገውን 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ውሳኔ ደረሰን፡፡ ፓርቲያችን ሁለቱን ደብዳቤዎች መሰረት አድርገን ከቦርዱ ፅ/ቤት ኃላፊ ጋር ባደረግነው ውይይት ቦርዱ በጥቅምት 20 ላቀረባቸው ጥያቄዎች መልስ ስጡ ዋናውም የቦርዱ ጥያቄ ነው ተብለን በመግባባት መንፈስ ተለያየን፡፡ ቦርዱ ጥቅምት 19 ተሰብስቦ ለፓርቲያችን ያቀረበልን ጥያቄዎች፤
1.      ሪፖርቱ ለምን 7 ወር ዘገየ፤
2.     የጠቅላላ ጉበዔ አባላት ቁጥር በደንቡ ውስጥ የለም እና
3.     የፕሬዝዳንት መረጣ ለማድረግ ጠቅላላ ጉባዔ ለብሔራዊ ምክር ቤት ውክልና የሰጠበት አግባብ ከዲሞክራሲያዊነት እና ከአባላት ተሳትፎ አንፃር ማብራሪያ ይፈልጋል፤
የሚሉት ናቸው፡፡
ለእነዚህ የቦርዱ ጥየቄዎች እና ጥቅምት 19  በቦርዱ ምክትል ኃላፊ ለቀረቡት ህገወጥ ጥያቄዎች መልስ አዘጋጅተን ጥቅምት 21 2007 ዓ.ም ለቦርዱ ፅ/ቤት ገቢ አደረገን፡፡
ህዳር 10 -19/2007፤
የምርጫ ቦርድ በጥቅምት 20 ላቀረባቸው ጥያቄዎች በጥቅምት 21 ለሰጠነው መልስ ገምግሞ የሚከተሉትን ውሳኔዎች የያዘ ደብዳቤ ህዳር 10 2007 ዓ. ም ለፓርቲያችን እንዲደርስ አደረገ፡፡ እነርሱም
1.      ሪፖርት መዘግየቱ አግባብ ያለመሆኑን ጠቅሶ ለወደፊት ሪፖርቶች በወቅቱ ገቢ እንዲደረግ
2.     የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ቁጥር ተወስኖ በደንብ ውስጥ መግባት እንደሚያስፈልግ እና
3.     የፕሬዝዳንቱን ምርጫ አስመልክቶ ጠቅላላ ጉባዔው ለብሔራዊ ምክር ቤት ውክልና የሰጠበትን አግባብ በቅንንት እንደሚያየው ገልፆ፤
በተራ ቁጥር 2 ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ ሲቀርብ ውሳኔ እንደሚሰጥ የሚጠቅስ ነበር፡፡
ህዳር 11 ቀን 2007 ዓ.ም የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ቁጥር 320 እንደሆነ እና ከዚህ ውስጥ 161 ሲገኝ (ሃምሳ ከመቶ በላይ)ምልዓተ ጉባዔ እንደሆነ ገልፀን ለቦርዱ አስገባን፡፡ በዚሁ መሰረት መልስ ይሰጡናል ብለን ስንጠብቅ፣ በቦርዱ በኩል ደግሞ ዝምተው ስበረታብን የቦርዱን ፅ/ቤት ኃላፊ እንዲሁም የቦርዱን ሰብሳቢ ሰናነጋግር ደንብ የሚሻሻላው በደብዳቤ ሳይሆን ይህን ማድረግ በሚችለው በጠቅላላ ጉባዔው መሆኑን በተዘዋዋሪ ገለፁልን፡፡ በዚህ ውይይት ዘወትር የሚሰጠን ምክር አርፋችሁ ለምርጫ ዝግጅት አድርጉ እኛ በቅንንት ነው የምናየው የሚሉ የማግባቢያ ንግግሮች ነበሩት፡፡ ይህንን ግን በፅሁፍ እንዲያደርጉት ባደረግነው ጉትጎታ ህዳር 19 ቀን ቦረዱ ያለውን የመጨረሻ ጥያቄ በፅሁፍ ሰጠን፡፡ ይኽውም የጠቅላላ ጉባዔ አባላትን ቁጥር በደንብ ውስጥ አካቱና አምጡ የሚል ነው፡፡ ቦርዱ ከዚህ በኋላ ባደረገው የደብደቤ ልውውጥ የህዳር 10 እና ህዳር 19 ደብዳቤ ሆን ተብሎ አይጠቅስም፡፡ የቦርዱን ቅንነትና ሆደ ሰፊነት የሚለውን አባባል ያልተመቻቸው አባላት ጠቅላላ ጉባዔ አባላት ተጠርተው ለጉዳዩ መቋጫ ለመስጠት በመወሰን ጉባዔ እንዲጠራ ተወሰነ፡፡
ታህሳስ 3-4፤
የአንድነት ፓርቲ በቦርዱ በቀረበለት ጥያቄ መሰረት የጠቅላላ ጉባዔ ኮረም በደንብ ውስጥ ለማስገባት ብቻ መጥራት ተገቢ አይደለም በሚል እምነት ከጉባዔ አባላት ቁጥር ከማካተት በተጨማሪ ያሉ የዞን አመራሮችን ጨምሮ በምርጫ ጉዳይ ላይ ሰፊ ውይይት የሚያደርግበት በፓርቲያችን ላይ በምርጫ ቦርድ በኩል በሚዲያ እየተፈጠረ ያለውን ብዥታ ለማጥራት የሚያሰችል ደማቅ ጉባዔ ተካሄደ፡፡ መፈክራችንም “ምርጫ 2007 ለለውጥ” የሚል ነበር፡፡ በኢትዮጵያ የተቃዋሚዎች ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሸበረቀ ጉበዔ አካሄደን የሚከተሉትን ውሳኔዎች ጉባዔ አሳለፈ፤
1.      የጠቅላላ ጉባዔ አባላት ቁጥር 320 እንዲሆን እና ኮረም 50 ከመቶ ሲደመር አንድ እንዲሆን፤
2.     የብሔራዊ ምክር ቤቱ የፓርቲውን ፕሬዝዳንት ለመምረጥ የሄደበት መንገድ ህገ ደንባዊ መሆኑን፤
3.     በቀጣይ ምርጫ ቦርድ በጠቅላላ ጉባዔው ውሳኔ ላይ ጥያቄ የሚያነሳ ቢሆን ብሔራዊ ምክር ቤቱ የጠቅላላ ገባዔውን ወክሎ ምላሽ እንዲሰጥ የሚሉት፤
ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡
ታህሳስ 10፤
የጠቅላላ ጉበዔውን ሪፖርት ታህሳስ 10 ቀን 2007 ዓ.ም ለቦርዱ ፅ/ቤት ገቢ የተደረገ ሲሆን ቦርዱ ይህንን ችላ በማለት ፍፁም ኃላፊነት በጎደለው ሁኔታ በዕለቱ ምሽት የቦርዱ ኃላፊዎች በሚዲያ ቀርበው በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ችግር እንዳለ የሚገልፅ መግለጫ ይሰጣሉ፡፡ በማግስቱ ቅዳሜ ደውለው ደብዳቤ እንድንወስድ ይነግሩናል፡፡ በታህሳስ 10 ቦርዱ ተሰብስቦ በወሰነው መሰረት የጠቅላላ ጉባዔ ሪፖርት በ7 ቀን ውስጥ እንድታስገቡ የሚል ነበር፡፡ ይህን ደብዳቤ አስመልክቶ እና በሚዲያ የሰጡትን መግለጫ አስመልክቶ ከቦርዱ ስብሳቢ ጋር ባደረግነው ውይይት ያቀረብነውን ሪፖርቱን በአጭር ጊዜ ተሰብሰበው ውሳኔ እንደሚሰጡት መግለጫ በክፋት ሳይሆን በቅንንት እንደሆነ ይገልፁልናል፡፡ ይህ እንደማይሆን ግን ምልክቶች እያየን ነበር፡፡ የቦርዱ ፅ/ቤት ኃላፊና ምክትላቸው በተለያየ መልኩ ከፓርቲያችን ውስጥ ቅሬታ ተሰምቶናል የሚሉ ህገወጦች ጋር በቢሮዋቸው እንደሚዶልቱ እየሰማን ነበር፡፡ በግንባርም በኃላፊው ቢሮ ከግለሰቦቹ ጋር ሲመክሩ አግኝተናቸዋል፡፡
ታህሳስ 27 -30፡
ቦርዱ ተሰብሰቦ ያቀረብነውን ሪፖርት መርምሮ መልስ ይሰጣል ብለን በቅንንት ስንጠብቅ ታህሳስ 26 እሁድ በስልክ ተደውሎ የቦርዱ ኃላፊዎች ለውይይት እንደሚፈልጉን ይነገረናል፡፡ የዚያኑ እለት እሁድ በፓርቲያችን ለሆዳቸው ያደሩ ባንዳዎች አራት ኪሎ በሚገኝ ካፍቴሪያ ተሰብሰበው ፊርማ ተፈራርመው ለቦርዱ ገቢ አድርገዋል፡፡ በእሁድ ቀን ማለት ነው፡፡ ታታሪው ምርጫ ቦርድ አንድነትን ለማናጋት እሁድን ጨምሮ ሌት ከቀን ይሰራል፡፡ ታህሳስ 27 ቀን 2007 ዓ.ም ቦርዱ ፅ/ቤት ስንገኝ ካሜራ ደቅነው ከአቶ የማነአብ አሰፋ እና ከአቶ አየለ ሰሜነህ ጋር “ውይይት” እንድናደርግ ግብዣ ያደርጉልናል፡፡ ዓላማው በምሽት ቦርዱ ሊሰጠው ላሰበው ውዥንብር መፍጠሪያ መግለጫ የቪዲዮ ግብዓት ለማግኘት የነበረ ሲሆን መኢህአዶች በየዋህነት በቪዲዮ ተቀርፀው ሲቀርቡ እኛ ከእነዚህ ሰዎች ጋር በምርጫ ቦርድ መድረክ የምናደርገው ውይይት እንደሌለ፤ ቦርዱ ያሰገባነውን ሪፖርትና ግለሰቦች ያቀረቡትን ሪፖርት መርምሮ ውሳኔውን እንዲያሳውቅ ብቻ መሆኑን ገልፀን ተመለስን፡፡ በምሽቱ የቦርዱ ምክትል ሰብሰቢ የውስጥ ችግራቸውን እንዲፈቱ ልናስማማቸው ሞክረን አልተሳካም፤ የታህሳስ 19-20 ሪፖርት 7 ወር አዘግይተው አስገብተዋል፤ የፕሬዝዳንቱ ምርጫ ህገወጥ ነው፤ የሚሉ መግለጫዎችን በመስጠት ህዝቡን ብዥታ ውስጥ ለመክተት ሞከሩ፡፡ ይህን ሲያደርጉ ቦርዱ ስብሰባ የተጠራው ለታህሳስ 28 ሲሆን ቦርዱ ከመሰብሰቡ በፊት በቅድሚያ በማን አለብኝነት የቦርዱ ምክትል ሰብሰቢ የግል ውሳኔያቸውን አስታውቀው ለቀሪዎቹ የቦርድ አባላት ዋጋ ቢስነት በህዝብ ፊት አረጋገጡ፡፡
በታህሳስ 28 በምሳ ሰዓት ተደውሎ የቦረዱን ውሳኔ ለመስማት በ9፡00 ሰዓት እንድንገኝ ጥሪ ተደርጎልን ስንሄድ ገዛኽኝ አዱኛ የሚባል የወረዳ ስድሰት አባል እና እራሱን የወረዳ ሰድስት ዕጩ አድርጎ ያቀረበ 10+1 ያጠናቀቀ እና ሰፊው የሚባል የወረዳ 7 አባልና አራሱን ለ2007 ምርጫ የወረዳ 7 ዕጩ አድርጎ አቅርቦ ያልተሳካለት አኩራፊ አኩራፊ የአንድነት አባላትን ወክለው እንዲገኙ በአኩራፊዎች ተወክለው ነበር፡፡ ይህ ቡድን ምርጫ ቦርድ ከመምጣቱ በፊት በአምባሳደር መናፈሻ ድራፍት ቢራ እየተጎነጩ በአቶ ትዕግሰቱ አውሎም መመሪያ ሲሰጣቸው ነበር፡፡
ቦርዱ ፅ/ቤት ያለውን ሁኔታ ስንረዳው አሁንም ለኢቲቪ የቪዲዮ ግብዓት ለማግኝት ካልሆነ ትርጉም እንደሌለው በመረዳታችን የቦርዱ ውሳኔ በፅሁፍ እንዲሰጠን ጠይቀን ወደ ቢሮዋችን ተመለስን፡፡ በምሽት ዜና እና በቅርቡ በከፍተኛ ወኔ ገዢውን ፓርቲ ለመከላከል የቆመው የኢህአዴግ ሚዲያ የሆነው ሬዲዮ ፋና የቦርዱ ውሳኔ ነው ያሉትን ነገር ግን ቦርዱ ከመሰብሰቡ በፊት በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ በሚዲያ የተነገረውን ውሳኔ በትንተና አቀረቡት፡፡ የቦርዱ ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መርጊያም ከንፈራች እስኪደርቅ ድረስ አንድነት ላይ አለ የሚሉትን ክስ ሁሉ አዘነቡት፡፡ ታህሳስ 29 የገና በዓል በመሆኑ ታህሳስ 30/ 2007 ጠዋት ማልደን ምርጫ ቦርድ ተገኘተን በሚዲያ የነዙትን ክስ በፅሁፍ እንዲሰጡን ስንጠይቅ ደብዳቤ እየተዘጋጀ እንደሆነ ገልፀውልን በ5፡00 ሠዓት ደብዳቤ ሰጡን፡፡ አባላቶቻችን ቁጭ ብሎ ተረቆ የተፃፈ ደብዳቤ አስገራሚው በሆነ ሁኔታ በታህሳስ 28 ተደርጎ ወጭ እንዲሆን ተደርጎ ቀን ተፃፈበት፡፡ እዚህ ጋ የቦርድ ኃላፊዎች የበታች ሰራተኞችን ምን ያህል ከህግ ውጭ እንደሚያሰሩ ነው፡፡ የቦርዱ ፅ/ቤት ምን ያህል ለመዋረድ እንደተዘጋጀ የሚያሳይ ነው፡፡ ለማነኛውም ታህሳስ 30 የደረሰን ደብዳቤ አራት ነጥቦች ያሉት ለማስመስል ቢሞክርም ሁለት ጥያቄዎች ናቸው ያሉት፡፡ እነርሱም
1.      የታህሳስ 19-20 ሪፖርት ለምን ዘገየ የሚል እና
2.     የፕሬዝዳንቱ ምርጫ የፓርቲውን ህገ ደንብ የተከተለ አይደለም የሚል ነው፡፡
የሚያሳዝነው ነገር ቦርዱ የታህሳስ 3 ቀን 2007 ጠቅላላ ጉባዔ ሪፖርት ለመመርመር ተሰብሰቦ የታህሳስ 19-20/2006 ሪፖርት ለምን ዘገየ ማለቱ ብቻ ሳይሆን በቅንንት ተቀብዬዋለሁ ያለውን የፕሬዝደንት ምርጫ በድጋሚ ማንሳቱ ነው፡፡ በግልፅም ቦርዱ የአንድነትን ሪፖርት በጥልቀት ገመገምኩ ይበል እንጂ እንዳልገመገመው ማሳይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ቦርዱ ወሰነ የተባለው እና የቦርዱ ምክትል ሰብሰቢ ከቦርዱ ስብሰባ በፊት በሚዲያ የሰጡት መግለጫ መመሳሰል ብቻ ሳይሆን ቦርዱ ሊመረምረው ከተቀመጠው ሪፖርት ይዘት የወጣ ውሳኔ አሳለፈ መባሉ ነው፡፡
ስለዚህ የታህሳስ 19-20/2006 ሪፖርት ለምን ዘገየ ከአሁን በፊት በቂ መልስ ተሰጥቶታ ቦርዱ እንደተቀበለው ማስታወስ እና አንድነትም በተከታይ ባደረገው ጠቅላላ ጉበዔ በሰባት ቀን ሪፖርት ማስገባቱ ነው፡፡
ጥር 1-3፤
አንድነት ፓርቲ ለመጨረሻ የደረሰው ደብደቤ ጥር 1 ቀን 2007 ከሰዓት በኋላ  11፡45 (ከሰራ ሰዓት ውጭ) የደረስን ህገወጥ ደብዳቤ በጥር 3/ ለሚደረገው ጠቅላላ ጉባዔ የምርጫ ቦርድ ታዛቢ መላክ እንደማይችሉ ገልፀው ለዚህም የሰጡት ሰበብ በእነ አየለ ሰሜነህ የሚመሩ አባላት ሌላ ጠቅላላ ጉባዔ በሳሬም ሆቴል በመጠራቱ ሁለት ቦታ ጉባዔ ታዛቢ መላክ አልችልም የሚል ነው፡፡ በመሰረቱ የምርጫ ቦርድ በእጁ በሚገኝው የፓርቲያችን ደንብ  አባላት ጠቅላላ ጉባዔ ሊጠሩበት የሚችሉበት ስርዓት በግልፅ ተቀምጦ እያለ ከዚህ ውጭ የፓርቲውን ጉባዔ ለማደናቀፍ ምን ያህል እየተሰራ እንደሆነ ግልፅ ማሳያ ነው፡፡ አንድነት በማግስቱ መገኘት ባይፈልጉም ጉባዔው በተያዘለት ፕሮግራም መሰረት እንደሚቀጥል ጥር 2/2007 እንዲያውቀት ተደርጎዋል፡፡ በዚሁ መስረት አድነት ጥር 3/2007 በደማቅ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ይህን መስመር የፃፍኩት ጉባዔዬው አሰመራጭ ኮሚቴ ሰይሞ ሲያጠናቅቅ ነው፡፡ ትግሉ ይቀጥላል……….. የደብዳቤው ልውውጥም ይቀጥላል፡፡ ይህ ታሪካዊ ዘገባ ይሆናል፡፡

ግርማ ሠይፉ ማሩ  (ጥር 3/ 2007)