Tuesday, August 26, 2014

በጥፍሩም በጥርሱም ለስልጣን የሚተጋ መንግሰት …… እንዴት እንታገለው!!

በጥፍሩም በጥርሱም ለስልጣኑ የሚተጋን መንግስት በሁሉን አቀፍ ትግል መጣል አለብን ብለው ጠብ መንጃ ቢያነሱ ክፋቱ ምን ላይ እንደሆነ አልታይህም እያለኝ ነው፡፡ ለምን በጠብ መንጃ ፍልሚያ ስልጣን መያዝ እንዳለብኝ በግሌ ባይገባኝም አሁን ግን የኢህአዴግ ዓይነት መንግሰት ከደርግ እንዴት እንደሚሻል ማሰብ እያቃተኝ ነው፡፡ የሰላማዊ ትግል ሰራዊት እንዴት እንገንባ ለሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምለሽ ካልሰጠን በስተቀር መንግሰት በግልፅ እየደገፈ ያለው በጠብ መንጃ ሊገዳደሩ የፈለጉት ነው፡፡ በሰላም ያልነውን ሰላም እየነሳን ይገኛል፡፡ መንግሰት ሆይ ሰላም እንድትሆን ሰላም ሰላም ለምንል ዜጎች ሰላም ሰጠን የምር የቀረበ ጥያቄ ነው፡፡
በፍትሕ አደባባይ የፈለገውን ማድረግ የወሰነ መንግሰት በእጅ አዙር ደግሞ በየማተሚያ ቤቱ እየሄደ መፅሄትና ጋዜጣ ታትሙና ወዮላችሁ ማለት ተያይዞታል፡፡ ይህ ከህግ ሰርዓት ውጭ በየማተሚያ ቤቱ በግንባር እና በስልክ የሚደረገው ማሰፈራሪያ ከወሮበላነት ውጭ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ መንግሰት ለህዝብ ጥቅም ሲባል ክስ መስርቻለሁ ብሎዋል፡፡ ህዝቡ የሚለው ግን ሌላ ነው፡፡ መፅሄት መቼ ነው የሚወጣው ነው፡፡ በቃ!!! ፍርድ ቤት በመፅሔትና ጋዜጦች ላይ ቢፊልግ እግድ ቢፈልግ ይዘጉ እሰኪል ድረስ ምን የሚያጣድፍ ነገር መጥቶ እንደሆነ ባናውቅም የመንግሰት አሽከሮች በየጉራንጉሩ ባሉ ማተሚያ ቤቶች ደጃፍ እየዞሩ ማሰፈራራት ተያይዘውታል፡፡ ሹሞቻችን ይህን አላደረግንም ብለው እንደሚክዱ ባውቅም ይህን ዓይነት ወሮበላነት ማስቆም ካልቻሉ ተጠያቂ እንደሚሆኑ መርሳት የለባቸውም፡፡ ስህተታችውን በአደባባይ ተችተን እንዲታረሙ የሚሰጣቸው ምክር ካንገሸገቸው የመጨረሻው ቀን ሲመጣ እንደሚጠየቁ ግን ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ የወሮበላ አለቃነት ከወሮበላነት በላይ የሚያስጠይቅ ነው፡፡ እነዚህን ወሮበላዎች አስቁሙልን ግልፅ አቤቱታ ነው፡፡ በየሳምንት ብዙ መቶ ሺ ብር ገቢ ያገኙ የነበሩ ማተሚያ ቤቶች በህጋዊ መስመር ሳይሆን በስልክና በቃል ከወሮበሎች በሚሰጥ ማሰፈራሪያ አጅ መስጠት እና ገበያ ማባረር ደግሞ የሚያስመሰግን ፍርሃት እንዳልሆነ ልብ ሊሉት ይገባል፡፡ የእያንዳንዳችን ፍርሃት ተደምሮ ነው እነርሱም ያለምንም ይሉኝታ ሊያሰፈራሩን ቤታቸውን ድረስ የሚመጡት፡፡ በወረቀት ትዕዛዝ ይድረሰኝ ለማለት ወኔ የሌለው ማተሚያ ቤት የሙት ዓመትና ተዝካር ወረቀት ሲያትም ይኖራታል፡፡
መንግሰት በሚዲያዎች ላይ በዶክመንተሪ ጀምሮት የነበረውን ወደ ፍትህ አደባባይ ያመጣውን የግል ሚዲያ አሁንም ገና አልበቃውም፡፡ በጥፍርም በጥርስም ሊዘለዝል እየባተተ ይገኛል፡፡ ኢትቪ ቤታችን ድረስ መጥቶ ለሆዳቸው ባደሩ ምሁራን ተብዬዎች እና ሹመኞች ሲሳደብ ያመሻል፡፡ የኮሚኒኬሸን ጉዳዮች መስሪያ ቤት ውስጥ ዳይሬክተር ናቸው የተባሉ ታምራት ደጀኔ የሚባሉ ኃላፊ መሰሪያ ቤቱ የመንግሰት ደሞዝ የሚከፈላቸው እኔ ጭምር በምከፍለው ግብር መሆኑን ዘንግተው የግል ፕሬስ ከተቃዋሚዎች ጋር ወግኖ እየሰራ ነው ብለው ከገዢው ፓርቲ ጎን ቆመው ሲከሱን አምሽተዋል፡፡ እኚህ ግለስብ ከተቃዋሚ ጎን መሰለፍ ማን ሀጥያት ነው እንዳላቸው አላውቅም፡፡ ተቃዋሚዎች በህግ ተመዝግበው የሚሰሩ ተቋማት እንደሆኑ እና የሚደግፋቸውም የሚቃወማቸውም ሰዎቸ መኖራቸው የሚጠበቅ መሆኑን ዘንግተውታል፡፡ ለነገሩ እርሳቸው የሚደግፉት ፓርቲ ነገ ተቃዋሚ የሚባል ወንበር ላይ ሊኖር እንደሚችል በተሰፋ ደረጃ ማሰብ አልቻሉም፡፡ ለነገሩ ኢህአዴግ በጥቅም የተገዙ አባላቶቹ ስልጣን ሲያጣ አብረውት እንደማይቆዩ ይረዳዋል- እርሳቸውንም ጨምሮ ማለቴ ነው፡፡ ለዚህም ነው ኢህአዴግ በጥርስም በጥፍርም ፍልሚያ ውስጥ የሚገባው፡፡ አቶ ታምራት ደጀኔ እንዲረዱ የምፈልገው የግሉ ፕሬስ ተቃዋሚን ቢደግፍ አንድም ነውር እንደሌለው ይልቁንም ገዢውን ፓርቲ ለመደገፍ ገዢው ፓርቲ ብቁ እንዳልሆነ ማሳያ ነው፡፡ ገዢው ፓርቲ በገንዘብ የሚደግፋቸው ነገር ግን ተደግፈው መቆም የማይችሉ “የግል” ተብዬ ሚዲያዎች እንደነበሩ መርሳት የለባቸውም፡፡ ለምሳሌ ኢፍቲን፣ ዛሚ፣ ወዘተ
ሰኞ ነሃሴ 19/2006 በቀረበው ዶክመንተሪ ተብዬ ዘባተሎ ላይ ከለየላቸው የመንግሰት ሹሞኞች እስከ ዩኒቨርሲት መምህራን አልፎ ተርፎም አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴን ያሳተፈ ነበር፡፡ እርገጠኛ ነኝ ሀይሌ በሚዲያ ላይ ስለሚታዩ ግድፈቶች አጠቃላይ ሁኔታ ነበር የሚናገረው እንጂ አሁን ክስ ስለተመሰረተባቸው የግል ሚዲያዎች አልነበረም፡፡ ቆርጦ ቀጥሉ ኢቲቪ ግን ከህዝብ ጋር ሊያጋጨው ፍላጎቱን አሳይቶዋል፡፡ ሌላው ተዋናይ ዶክትረ አሸብር ወልደጊዮርጊስ ነበሩ፡፡ ከብዙ ጊዜ በተሻለ ሁኔታ ነበር መልስ አሰጣጣቸው፣ የከሰሱትም ሪፖርተርን ነው፡፡ መንግሰት ደግሞ ከሪፖርተር ጋር ጉዳይ የለውም፡፡ እንዲከሱ ሲጠበቅ የነበረው ሌላ ነበር፡፡ ይቅር ብያለሁ ብለው አልፈውታል፡፡ የእርሳቸው ይቅር ባይነት ከመንግሰት ሰፈር ሊገኝ አልቻለም፡፡ ተበቃይ መንግሰት ለስልጣኑ ሲል በጥፍሩም በጥርሱም ከግል ሚዲያው ጋር ግብ ግብ ገጥሞዋል፡፡ ማን ያሸንፋል አና መቼ ወደፊት የሚታይ ነው፡፡
የቀረበውን ዘጋቢ ፊልም ማስታወሻ ይዜ ለሁሉም በስማቸው አንፃር ለመፃፍ ነበር የፈለኩት ይህን ዘባተሎ የበዛበት ድሪቷም ዘጋቢ ተብዬ ከዚህ በላይ ማለት ተገቢ ሆኖ ስለአልተመቸኝ ተውኩት …. ይህ ዘጋቢ ፊልም ተብዬ የተሰራበት ሙሉ ዶክመንት ለታሪክ እንደሚቀር ተሰፋ አለኝ፡፡ የዛን ጊዜ እንወቃቀሳለን፡፡ ምሁራን ተብዬዎች በእናንተ ተሰፋ ቆርጠናል ….. በእናንተ መምህርነት አንድም የተሻለ ጋዜጠኛ እንደማናገኝ፡፡ ለነገሩ ልጆቹ የአስተማሪዎች ብቻ ሳይሆን የእኛም ናቸው እና በቤታችን ይማራሉ፡፡ ሀገር ማለት ልጄ ብለን እናስተምራለን፡፡


Sunday, August 17, 2014

የግል ሚዲያዎች ክስ ለምን?


በዚህ የፋክት ዕትም ከ“ግል ሚዲያ” ውጪ ስለ ሌላ ነገር መፃፍ ትክክል መስሎ አልታየኝም፡፡ ይህን ሳስብ ደግሞ ባለፈው ዕትም በፋክት መፅሔት በከፊል የተነሳውን የኢህአዴግ የፖሊሲ ወረቀት “የዴሞክራሲ ሰርአት ግንባታ ትግልና አብዮታዊ ዲሞክራሲ” በሚል በመጋቢት 1999 ዓ.ም የወጣውን መሰረት ማድረግ ወሰንኩ፡፡ ከዚህ የፖሊሲ ወረቀት ውስጥም “ሚዲያና ዲሞክራሲ” በሚለው ንዑስ ርዕስ ላይ አተኩራለሁ፡፡ ለዚህም ምክንያቴ፣ አሁን መንግስት እንደሚለው እየወሰደ ያለው እርምጃ  ህግን የማስከበርና የህዝብ ጥያቄን የመመለስ ሳይሆን፤ በፖለቲካ ሰነዱ ላይ ያስቀመጠውን በግል ሚዲያዎች ላይ መወሰድ ያለበት ተከታታይ እርምጃ ክፍል መሆኑን በመጥቀስ ይህን የፖለቲካ ሰነድ አግኝተው ለማንበብ እድል ላልገጠማቸው አንባቢያን ማስረዳት ነው፡፡ ከዚያም በማስከተል ይህ ሰነድ፣ በፈለገው መንገድ ተተርጉሞ ህገወጦች ይለናል በሚል ነፃነታችንን አሳልፈን ለመስጠት አለመዘጋጀታችንን ይፋ ለማድረግ ነው፡፡ ነፃነት በነፃ አይገኝምና፡፡
ይህ የምርጫ 97 ዝረራ የወለደው የፖለቲካ ሰነድ ሚዲያን በሚዳስስበት ንዑስ ክፍል መግቢያ ላይ “ሚዲያ የዴሞክራሲ ስርአትን በመገንባት ረገድ ወሳኝ ድርሻ ካላቸው ተቋሞች አንዱ ነው” ብሎ የሚጀምር ቢሆንም፤ ዋና ግቡ ግን ሚዲያን እንዴት ማጥፋት እንደሚቻል የሚተነትን ነው፡፡ የሩዋንዳን እልቂት ፈጣሪ ሚዲያዎችን ፣ የምዕራባዊያንን የሚዲያ ተቋማትን እንዲሁም በአረቡ ዓለም ያሉትን አልዓረቢያና አልጀዚራን የመሳሰሉ ሚዲያዎችን በመጠቃቀስ “ኪራይ ሰብሳቢ ሚዲያዎች” የሚል ፅንሰ ሀሳብ ለማዋለድ በሚረዳ መልኩ “የኪራይ ሰብሳቢነት ፖለቲካ ኢኮኖሚ በልማታዊ ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ በተሟላ መልኩ መተካት አለበት” ብሎ ይደመድማል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በኋላ ኪራይ ስብሳቢ ሚዲያ ሲባል አቤት ማለት ይኖርብናል፡፡ ልዩነት ለዘላለም ይኑር ብለን የምንዘምር ሰዎች የኢህአዴግ “ልማታዊ ፖለቲካው ኢኮኖሚ”ን እንደ አንድ አስተሳሰብ መቀበል ብንችል እንኳን፣ ይህን አስተሳሰብ ለራሳችን ለማድረግ የምንቸገር ሰዎች አለን፡፡ ይልቁንም ከዚህ የተሻለ አማራጭ አለን ስንል፣ ይህ አስተሳሰብ በኢህአዴጎች ሰፈር “ኪራይ ስብሳቢነት” ቢሆንም በነፃነት ልናራምድ የምንችልበትን መድረክ ለመንፈግ፣ ይህ ሰነድ የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም፡፡
የሚዲያ ነፃነትና የዲሞክራሲ ስርአት ግንባታን በሚመለከት የፖለቲካ ሰነዱ  “ሚዲያውን በነፃነትና በጤናማ አኳኋን እንዲያድግ ማድረግ ለማንም ሲባል የሚሰራ ስራ ሳይሆን በአገራችን የዴሞክራሲ ስርአትን እውን ለማድረግ ተብሎ የሚከናወን በመሆኑ ለሌሎች የዴሞክራሲ ሰርአት ግንባታ ስራዎች ከምንሰጠው ትኩረት የማይተናነስ ትኩረት ለዚህም ስራ መሰጠት አለበት” ይላል፡፡ ይህን አባባል በጥሬው ስንመለከተው ምንም ክፋት የለበትም፡፡ ነገር ግን ምን ዓይነት ‹ነፃነት› እና ምን ዓይነት ‹ጤንነት› እንደሆነ ስንመረምር ችግሩን መረዳት ይቻላል፡፡ ኢህአዴግ ሌሎችንም የዴሞክራሲያዊ ተቋማትን ማለትም የብዙኃን ማኅበራትን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የህዝብ ምክር ቤቶች እንዲሁም የዳኝነት ስርዓቱን ምን ያህል ነፃነት እየከለከለ ጤና እንደሚነሳቸው ስንረዳ፣ ምን ዓይነት ነፃነትና ጤና እንደታዘዘልንም መረዳት ቀላል ነው፡፡ የግል ሚዲያውም ከላይ እንደገለፅኳቸው የዴሞክራሲ ተቋማት ሸፋፋ እንዲሆን የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንገኛለን፡፡ ስለዚህ ኢህአዴግ ሚዲያውን እንደሌሎቹ የዲሞክራሲ ተቋማት ሙት እንዲሆን መፈለጉን እንረዳለን፡፡ በሙታን ውስጥ የሚገኝን ነፃነት እና ጤና የሚያውቁት ሙታኖች ብቻ ናቸው፡፡
ኢህአዴግ እንደ መንግስት የሚዲያውን አቅም መገንባት ሳይሆን እንዴት አድርጎ መዋጋት እንዳለበት በዝርዝር አስቀምጧል፡፡ ይህንንም ለማድረግ በፖለቲካ ሰነዱ ውስጥ የተቀረፀውም በአቅም ግንባታ ሞዴል ሳይሆን በውጊያ ሞዴል ነው፤ “ኪራይ ስብሳቢነትን መዋጋት” በሚል ርዕስ ነው የተቀመጠው፡፡ በዚህ ንዑስ ርዕስ ስር በዋነኝነት የተቀመጠው የውጊያ ግንባር “የሚዲያ አውታሮች ገቢና ወጪያቸውን በትክክል እንዲያስመዘግቡና በየጊዜውም ጥብቅ ቁጥጥር እንዲደረግበት ማድረግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡” ይላል፡፡ ይህም የሚረዳው “በውጭ ሃይሎችና በፀረ ሰላም ድርጅቶች ፋይናንስ እንዳይደረግ በጥብቅ መከላከልና መቆጣጠር በጣም አስፈላጊ ይሆናል፡፡” በሚል ነው፡፡ ይህን በተመለከተ በግል ሚዲያዎች ላይ ማስረጃ ማቅረብ የተሳነው መንግስት በቴሌቪዥን በኩል ለሆዳቸው ያደሩ ሹሞችን እና ባለሞያ ነን የሚሉትን ሰብሰቦ በዘጋቢ ፊልም ‹‹መረጃ አለን፤ ከሚያትሙት አርባ አምስት ሺ፣ ሁለት ሺውን ብቻ ነው የሚሸጡት›› የሚል ፕሮፖጋንዳ ለመስራት ይዳክራል፡፡ ማስረጃ ማቅረብ ያልቻለ መንግሰት ‹መረጃ› እያመረተ ይገኛል፡፡ ወደፊት እነዚህ መረጃዎች በማስረጃ ደረጃ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ብለን ብንጠረጥር አስገራሚ አይሆንም፡፡ ለነገሩ ያቃጥሉት ነበር የሚል አዳፍኔ ምስክር ይጠፋል ብላችሁ ነው፡፡
በዚህ መስመር አንድም ማስረጃ ማግኘት የተሳነው መንግስት፣ በቀጣይ በሚዲያ ተቋማት ላይ ከማስታወቂያ እና ከአንባቢ በሚገኝ ገቢ ላይ እርምጃ መውሰድን እንደ ዋነኛ የኢኮኖሚ ቁጥጥር ስርአት አድርጎ ይዞታል፡፡ አንባቢዎችም እንደምትረዱት የመንግስትና የግል ድርጅቶች ማስታወቂያ እንዳያወጡ ከፍተኛ ጫና በመዳረጉ አሁን ጥርስ የተነከሰባቸው መፅሔቶች ማስታወቂያ ሳያወጡ በመፅሃፍ መግዣ ዋጋ መፅሔት ለመሸጥ በመገደዳቸው መንግስት ወደ ሌላ እርምጃ ተሸጋግሯል፡፡ ሌላኛው እርምጃ ከሰሞኑ የተሰማው ክስ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ይህ ነውረኛ የፖለቲካ ሰነድ ጥርስ የተነከሰባቸውን የግል ሚዲያዎች የሚገልፃቸው ነውረኛ በሆነ አገላለፅ ነው፡፡ በኢህአዴግ ሰፈር መገበርም አያስከብርም፡፡ እነዚህ የግል ሚዲያዎች አብዮታዊ ዲሞክራሲን ባይቀበሉም የመንግሰትን ስትራቴጂ የተቀበሉ ኪራይ ስብሳቢዎች በማለት ይገልፃቸዋል፡፡ ለእነርሱም “በሕጉ መሰረት የሚሰሩ ጥገኞችን በተመለከተ ግን ለስራቸው የተመቻቸ ሁኔታ የመፍጠር አሰራር ልንከተል ይገባናል” በማለት ይሰድባቸዋል፡፡ በቅርቡ ለነዚህ ጥገኞች ምን ተጨማሪ ነገር እንደሚደረግላቸው የምናየው ይሆናል፡፡ እንደምታስታውሱት ለጥገኛ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጎማ ሲሰጣቸው፣ የሌሎቹ ፓርቲ አባላት ደግሞ በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡
በኢህአዴግ አብዮታዊ ዲሞክራሲ መስመር ያልገባ ሁሉ ህገወጥ እና ጤና የሌለው ተደርጎ ይቆጠራል፡፡ በዲሞክራሲ፣ ሰላም እና ነፃነት ላይ የቆመ ደንቃራም አድርገው ይቦድኑታል፡፡ ህዝቡ ኢህአዴግ የሚያወራውን ይህን ሽብርና መዓት ወደ ጎን በማለት ኪራይ ሰብሳቢ ለሚላቸው የግል ሚዲያዎች መተማመኛው የፈለገውን ያህል ውድ ቢሆኑ፣ ተሻምቶ በመግዛት የአለንላችሁ መተማመኛ መስጠቱ አልተዋጠላቸውም፡፡ ሹሞቻችን ይህን የህዝብ መተማመኛ ተቀብለው ለመሄድ ፈቃዳቸው አይደለም፡፡ ይልቁንም ከህዝብ ውጭ አለቃ የለንም እያሉ በየመድረኩ የሚገዘቱ ሹማምንት፤ ህዝብን በሚንቅ መልኩ፤ ‹በህዝብ ጥያቄ መሰረት በግል ሚዲያዎች ላይ እርምጃ ወስደናል› ይሉናል፡፡ ህዝቡ እርምጃው ለምን ተወሰደ ሳይሆን የሚለው ለምን ዘገየ እያለ ነው፡፡ ህዝቡ፣ ህዝቡ፣ ህዝቡ እያሉ በመንግሰት ሚዲያ ላይ ቀርበው ይዘባበታሉ፡፡
ለማንኛውም ከላይ እንደተረዳነው የኢህአዴግ የፖለቲካ ሰነድ የሚያስቀምጠው “ዋነኛው መቆጣጠሪያ መንገዱ ኢኮኖሚያዊ ስለሆነ … ልዩ ትኩረት ሰጥተን ልንረባረብበት ይገባል፡፡ ከዚህ ጎን ለጎን በህገወጥ ሚዲያዎች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድባቸው የሚደረገው ሂደት በአስተዳደራዊ ገፅታው ብቻ ሳይሆን በፖለቲካው ገፅታው መታየት አለበት፡፡” በማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ በምንም መመዘኛ የግል ሚዲያዎቹ በሀገርና በህዝብ ላይ ሽብር በመፍጠራቸው ሳይሆን በአብዮታዊ ዴሞክራሲ አስተሳሰብ ላይ በፈጠሩት ሽብር መነሻ ብቻ ነው፡፡ እርምጃውም ፖለቲካዊ በመሆኑ፣ ከቀጣዩ ምርጫ ጋር ተያይዞ በመጣ ፍርሃት የተነሳ ነው፡፡ ስለዚህ የግል ሚዲያዎች ለአብዮታዊ ዲሞክራሲ አንገብርም በማለታቸው “ህገወጥ” በሚል ሽፋን አስተዳደራዊ እርምጃ ለመውሰድ ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡ ከላይ ለመጥቀስ እንደሞከርኩትም፣ ይህ አቅጣጫ የተቀመጠው በመጋቢት 1999ዓ.ም ከምርጫ 1997 ሽንፈት ማግስት ነው፡፡
ይህ ጉደኛ ሰነድ “አስተዳደራዊ እርምጃ ተገቢ መሆኑን ህዝቡና ከዚያም አልፎ ብዙሃኑ የሚዲያው ተዋንያን የሚቀበሉበት ሁኔታ መፍጠር አለብን፡፡” ይላል፡፡ ለዚህ ነው እንግዲህ፣ መንግስት ወገቡን ታጥቆ እርምጃው ተገቢ ነው እያለ የሚሰብክን፡፡ ይህን ድራማ ለመስራት የሚጋበዙትም ሰዎች ይህን መረዳት ያለመቻላቸው አስገራሚ ነው፡፡ ሰነዱ በመጨረሻም “ለውጭው አለም በዚህ ረገድ የምንወስዳቸውን እርምጃዎች ተገቢነት ለማስረዳት ጥረት ማድረግ ያለብን ቢሆንም ጋዜጠኞች በምንም አይነት ምክንያት መታሰራቸውን የማይቀበሉ ሃይሎች በርካታ በመሆናቸው እነዚህን ለማሳመን ከመንገዳችን ወጥተን መሄድ የሚጠይቀን መኖር የለበትም፡፡” ብሎ ያጠናቅቃል፡፡ አንድም ጋዜጠኛ፣ ጋዜጠኛ በመሆኑ አይታሰርም በሚል ድርቅ ብለው የሚከራከሩን ሹሞቻችን ጋዜጠኞችን ለምን እንደሚያስሩ ግን በሰነዳቸው ላይ በፅሁፍ አስቀምጠዋል፡፡ ጋዜጠኞች የሚታሰሩት በጋዜጠኝነታቸው ብቻ ሳይሆን እንደ ሰው በያዙት አመለካከትም ጭምር ነው፡፡ ጥገኛ ለመሆን ባለመፍቀዳቸው እና ለነፃነታቸው በመቆማቸው ነው፡፡

እንግዲህ አስተዳደራዊውን እርምጃ ተከትሎ የሚመጣው  እስር መሆኑን ልብ ማለት አለብን፡፡ የዚያን ጊዜ ደግሞ ኢህአዴግ ከመስመር መውጣት ሳያስፈልገው “ጋዜጠኛ አላሰርንም፣ ጋዜጠኛ መሆን ወንጀል ለመስራት ሰርተፊኬት አይደለም” እያለ በመስመሩ ላይ ሆኖ ያላግጣል፡፡ ለማነኛውም በፖለቲካም ሆነ በጋዜጠኝነት ተሳትፎ የሚያደርጉ ሁሉ፣ የሚሳተፉት ይህ ጠፍቷቸው ሳይሆን ነፃነታቸው ከዚህ በላይ መሆኑን የሚረዱ በመሆናቸው ነው፡፡ ለነፃነት ሲባል ከእስርም በላይ ሞትን ለመቀበል የቆረጠን ሰው ማቆም እንደማይቻል መረዳት ግን ተገቢ እና አስፈላጊ ነው፡፡ይህን ፅሁፍ ለምታነቡ የኢህአዴግ አባላት አንድ ጥያቄ አለኝ፤ “ከጥገኝነት እና ከነፃነት” የቱ ይሻላል?

Monday, August 11, 2014

Salary Adjustment: Poor Planning Disappoints Everyone

In my commentary, headlined “Propaganda Zeroes Salary Increment” (Volume 15, Number 743, June 27, 2014), I used the phrases “government employees” and “civil servants” interchangeably to explain my position about the economic reasons for possible inflation related to the recently announced salary adjustment. Lately, however, I found it was wrong to use “government employees” and “civil servants” interchangeably.
I do not know how many of us clearly know the distinction between “government employees” and “civil servants”. In my view, the disappointing salary increment is a result of the different meanings to these names.
The politicians and bureaucrats at the civil service ministry and the Ministry of Finance & Economic Development (MoFED) were not in the same page in working out the salary adjustment. The bureaucrats have prepared a salary increment based on their definition of civil servants.
But the politician has dragged this salary adjustment to include government employees and beyond. Hence, the current salary adjustment is eroded not only by inflation, but also the scrambling due to the different definitions of names.
At the outset, unofficial sources leaked information that the salary increment has been expected to be at the range of 70pc to 100pc, the higher percentage going to low-earning civil servants. This was really sensible.
But following the wide-running expectation sparked by this information, the government officially rejected the information. Unlike the usual behavior of the EPRDF government, the denunciation came from a relatively by low-profile minister.
Why does EPRDF government muddled into such confusion?
For me, this muddling is due to lack of clarity in defining what constitute civil servants.
Are all civil servants government employees?
Not at all! Just after the announcement of the salary adjustment by the Prime Minister, a serious challenge overwhelmed the political corridor on whether to include the military or not. If this salary adjustment scheme is to include the military, it will not be for civil servants, but rather to all government employees.
That is why the expected increment reduced almost by half from the expected and leaked information. I presume the military took the slice from the civil servants.
After the surprise announcement of the salary adjustment, one of my friend, a journalist, asked me, “Does this adjustment include the military?” My answer was a prompt, no.
I said this because the prime minister, on the Civil Service Day, said that the increment is for civil servants. I said so also because I know there were salary adjustment to the military without any propaganda, based on organizational restructuring within the military and above all the salary scale and benefit scheme for the military is significantly different from the civil servants.
I do not see any good reason to mix up the civil service and the military. Later, however, I came to know that the salary increment includes the military. This is as a result of the possible expected grievance from the military that pushed the politicians to reduce a good share from the civil servant to distribute to the military.
That is why the current salary increment is not for civil servants but to all government employees and beyond. Sadly, it makes none of them happy.
This political decision was disclosed by the senior minister, Sufian Ahmed, at the Parliament session in his budget defense (not in the budget speech) in response for the question raised by one of the Members of Parliament (MPs), possibly a pre-designed question. In my unofficial discussion with some MPs regarding the current salary adjustment, however, they have failed to understand the clear distinction between government employees and civil servants.
Worse is that they have considered themselves as part of the government employee and claim to get salary adjustment.  For sure, they will get the salary increment. Unfortunately, even we, ‘elected’ representatives of the people, consider ourselves as government employees. It is shame on us!
Whatsoever the reasons for this small amount of salary adjustment, the civil servants are not happy.
Why is this salary adjustment disgusting?
Obviously, it does not compensate the eroded purchasing power of take-home money in the past three years. It also could not be taken as an opportunity for sharing the fruits of a 10-year consecutive double digit growth.
The government has claimed that we have become a nation with a per capita income of 550 dollars. But I do not know why the government wants to pay its employees well below the annual per capita income.
If it is true that we as a nation have achieved a per capita income of 550 dollars, then, the minimum salary after tax (net salary) should not be less than 1,000 Br. Anything less than this is exploitation by the government.
By the same token, then, the government should double the salary of low-earning government employees. I believe this is a justified inquiry.
Even then, it seems unfair to compare government and private employees at the professional level, not to say high-earning employees. Regarding the professional salary scale in the private sector, it is far above the government scale, even after the current salary adjustment.
The current proposed salary is less than one third of the private sector.
How could high-level professionals stay in the government sector, then, without engaging in unlawful activities that generate money?
What makes it all confusing is that the government, in principle, expects to retain high caliber professionals to pursue its duty of assuring standards and qualities, while paying them so much lower than their peers in the private sector.  
My point is that the current salary increment is not professionally done. It is not well-thought and consulted with stakeholders.
Had it been professionally done, it would have satisfied at least few groups. This unanimous contention of the increment, even before it reaches the pocket of government employees, coupled with possible inflation, relates to poor planning.
How could we get good governance out of disappointed public servants, then?
I do not expect satisfactory public service from discouraged civil servants.

- Girma Seifu Maru is a Member of Parliament (MP) from MEDREK. He can be contacted at girmaseifu32@yahoo.com. 

ድሬ ድሮ እና ዘንድሮ


ከአዲስ አበባ የሐምሌ ጭጋግ ለመሸሸ ከምጠቀምባቸው አማራጮች አንዱ ከወሩ አጋማሽ ጀምሮ ድሬዳዋ መገኘት እና የቁልቢ ገብርኤልን በዓል ትሩፋት መሻት ነው፡፡ እንደ አጋጣሚ ሆኖ በዚሁ ወር በጋምቤላ ለሶሰት ቀናት መገኘት በመቻሌ፤ የሐምሌን ጭጋግ ሽሽት በቆላዎቹ የሀገራችን ክፍሎች የማደርገውን ቆይታ የተሳካ አድርጎታል፡፡ የነበረንን ጉዞ አጠናቀን እግራችን ጋምቤላን ከመልቀቁ፤ በመዥንገር እና “ደገኞች” በሚባሉት ነዋሪዎች መካከል መፈጠሩ የተሰማው ግጭትና ደም መፋሰስ፣ ኢህአዴግ የዘራው የጎሰኝነት ፍሬ ማሳያ አንዱ ክፍል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡ ልብ በሉ! ኢትዮጵያዊነታችን ጥላ ሆኖን እንደልባችን መዘዋወር አንችልም፡፡ መጤ እና ነባር ተብዬ ፍልስፍና ነብስ ዘርቷል፡፡ በጋምቤላ ቆይታዬ የታዘብኩትን በሌላ ጊዜ ልመለስበት እችላለሁ፡፡ ለዛሬው ግን በድሬዳዋ እና አካባቢው የታዘብኩትን ላካፍላችሁ፡፡
በቁልቢ በዓል ላይ የሙስሊሙ እና የክርስቲያኑን አብሮነት ስመለከት፣ ለምን ይህን አብሮነት እና ሰላም የሚጠሉ ሰዎች ይፈጠራሉ? የሚል ጥያቄ ያጭርብኛል፡፡ ጥያቄዬውን ተከትሎ የሚመጣልኝ መልስ ደግሞ፤ በግላቸው ባላቸው ችሎታና አቅም የማይተማመኑ ነገር ግን ሰልጣን እና ጥቅም የሚሹ ወይም ደግሞ በአንድ አጋጣሚ ይህን ጥቅም ቀምሰው ጥቅም ያናወዛቸው “ልሂቃን” እና የአካባቢ ተወካይ ነን የሚሉ ግለሰቦች፤ በቡድን መብት ስም የሚፈጥሩት ውዥንብር እንደሆነ ግልፅ ሆኖ ይታየኛል፡፡ እንግዲህ በሀገራችን ሰላም የሚሰጠን፣ ለእነዚህ ጥቅም ላናወዛቸው ግለሰቦች፣ ልጓም ሲበጅ ነው ብዬም አምናለሁ፡፡ ይህን አብሮነታችንን ሰኞ ዕለት በነበረው የሙስሊሞች በዓል በድሬዳዋ ከተማ ተገኝቼ ተመልክቼዋለሁ፡፡ በቡድን መብት ስም ስልጣን ላይ ያሉት ወገኖች ግን ይህ ሰላም ዘላቂ እንዲሆን የሚሹ አይመስሉም፡፡ እናስተዳድረዋለን በሚሉት ከተማ እዚህም እዚያም የሚፈጥሩት ችግር፣ ሙስሊሙን እና ክርስቲያኑን የከተማ ነዋሪ እያማረረው ነው፡፡
ድሬዳዋ በቅርቡ የከተሞች ቀንን እንደምታስተናግድ እየተሰማ ነው፡፡ ከተማዋን ለማስዋብ በሚል ሰበብ በመንገድ ላይ የሚገኙ አጥሮች ቀለም እንዲቀቡ ቀጭን መመሪያ ተላልፏል፡፡ የመመሪያው መቅጠን ደግሞ መመሪያ አውጪውን አካል ትዝብት ላይ ጥሎታል፡፡ መመሪያው፣ “የሚቀባው የቀለም መለያ ቁጥር፣ የቀለም ቀቢውን ስልክ ቁጥር እና ስሙን ጨምሮ” እንደሚያስተላልፍ ያዛል፡፡ የሚገርም ጊዜ ላይ ደርሰናል ማለት ነው፡፡ ይህ ቀጭን ትዕዛዝ የደረሳቸው አንድ ባለሆቴል ሰውዬ “ቀለሙን አስቀባለሁ እነርሱ ላዘዙኝ ቀለም ቀቢ ግን አስቀብቼ መመሪያ አውጪዎቹ ኮሚሽን አይበሏትም” ነበር ያሉኝ፡፡ ህዝብ እንዲያስተዳድሩ በተለያዩ አጋጣሚዎች ቦታ የያዙ ሰዎች፣ ይህን ያህል የማሰቢያ አቅላቸውን የሚያስት የጥቅም ግንኙነት እንዴት ሊፈጥሩ እንደሚችሉ ማሰብ ይከብዳል፡፡ እንግዳ ሊመጣ ነው ቤት እናፅዳ ማለት የአባት ቢሆንም፣ በዚህ ደረጃ መመሪያ ማቅጠን ግን ምክንያቱ ግልፅ ነው፡፡
የድሬዳዋ ከተማ በፅዳት እጅግ ምስጉን እንደነበር ማንም ይመስክራል፡፡ ነበር ያልኩት ያለምክንያት አይደለም፡፡ አንደኛው ድሬዳዋ ውስጥ በአሁኑ ጉብኝቴ ከወትሮ በተለየ የፅዳት መፈክሮች በብዛት መመልከቴን ሲሆን፤ ሌላው ደግሞ በአጋጣሚ ወደ ጤና ቢሮ እና አካባቢው ጎራ ባልኩበት ጊዜ ከጤና ቢሮ 50 ሜትር ርቀት በማይሞላ ቦታ ላይ መንገድ ዘግቶ የተከማቸውን ቆሻሻ እና በየውሃ መውረጃ የሚታየው ፍሳሽ ድሬዳዋን የሚመጥን አለመሆኑን በመታዘቤ ነው፡፡ ወግ ደርሶን እኛም ድሮ ለማለት በቃን፡፡ ቆሻሻ የሚመጥነው ከተማ ባይኖርም፤ በፅዳት መፈክር ያበደችው ድሬ አሁን ለከተሞች ቀን ለታሰበው ጽዳት ቀድመን እናቆሽሻት በሚል የተጠመደች ትመስላለች፡፡ በተለምዶ “ፋይናንስ” ተብሎ ከሚታወቀው የከተማው አስተዳደር ምክር ቤት ከሚገኝበት መቶ ሜትር ርቀት ላይ አዲስ በሚገነባው ፍርድ ቤት ህንፃ አጥር ስር የተከማቸው ቆሻሻ የአዲስ አበባን “ቆሼ” ያስታውሳል፡፡ ይህ እንግዲህ ከተማውን ለሚያስተዳድሩ አካላት ከእይታ ውጭ ነው ለማለት አይቻልም፡፡ እነርሱ ከቀለም ቀቢ የሚገኝ ኮሚሽን ላይ አፍጥጠው፤ የከተማውን ቆሻሻ የሚያነሳ ጠፍቶ የተለያዩ ሰበቦችን ይደረድራሉ፡፡
ድሬ ሲታሰብ የከዚራ ጥላውንም ማንሳት ተገቢ ይመስለኛል፡፡ የድሬ ጥላ የነበሩት ዛፎች እየተመናመኑ፣ ቀድሞ የነበሩ ቤቶች እየፈረሱ፣ አዲስ ህንፃ በከዚራ ሊሰራ የፈረሱ ቦታዎች ታጥረው ይገኛሉ፡፡ በአስደናቂ ፍጥነት የተጠናቀቀው የዳሽን ባንክ ህንፃም እንደተጠበቀው ለከዚራ ድምቀት አልሰጠም፡፡ ለአንድ የባጃጅ ሾፌር “ህንፃዎቹ ሲያልቁ ከዚራ ይደምቃል” የሚል አስተያየት ስሰጠው፣ የመለሰልኝ መልስ ይበልጡኑ አስገርሞኛል፡፡ ሾፌሩ፣ “በሲሚንቶ ክምር ከተማ አይደምቅም” ነበር ያለኝ፡፡ ‹‹እንዴት?›› ብዬ ጥያቄዬን ሳስከትል “ድሬዳዋ ፎቅ ሳይሆን ሰው ነው የሚያስፈልጋት፤ ድሬዳዋ ማነው ፎቅ ላይ ወጥቶ የሚገበያየው?” ብሎ መልስ ሰጠኝ፡፡ ስለዚህ የድሬዳዋ ከተማ የነዋሪዎቿን ስነ-ልቦና ያገናዘበ ግንባታ መሻቱን ተረድቻለሁ፡፡ ይህ ታዲያ የማን ኃላፊነት ነው? ብዬ ብቻዬን ስቆዝም፤ የባጃጅ ሾፌሩ በሀዘን ስሜት እንዲህ አለኝ፤ “እነዚህ ሰዎች የድሮ ነገር አይወዱም፡፡ የነበረውን ባቡር ጣቢያ አፍርሰው ሌላ ይሰራሉ፤ ከዚራን አጥፍተው ሳቢያን እንዲለማ ይፈልጋሉ፡፡ የድሮ ከዚራ እንዲኖር የሚፈልጉ አይመሰለኝም፡፡” በእውነትም ከዚራን ማፍረስ ለምን ቅድሚያ ተሰጠው? የሚል ጥያቄ ማንሳት ያስፈልጋል፡፡
ከዚራን ከማፍረሱ ጎን ለጎን ደግሞ በዚያ አካባቢ በብዛት በሚገኙት የኪራይ ቤቶች ውስጥ ያሉ ነጋዴዎች አስተዳደሩ ሌላ ስጋት ጋርጦባቸዋል፡፡ ቀደም ሲል ሲከፍሉት የነበረውን በመቶዎች የሚቆጠር ኪራይ በመከለስ፤ ስምንትና አስር ሺ ብር እንዲከፍሉ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየሰራ እንደሆነ በከተማው ይወራል፡፡ አንዳንዶች ከምርጫ በፊት ተግባራዊ ላያደርጉት ይችላሉ የሚል ተስፋ ቢኖራቸውም፤ የማይቀር ዕዳ ነው የሚሉት ያመዝናሉ፡፡ ለምን መንግስት እንዲህ ያደርጋል ያልኳቸው አንድ ነጋዴ፤ “ለአባይ ግድብ ገንዘብ እስኪሞላ እኛ ማለቃችን ነው” የሚል ምላሽ ሰጥተውኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ነጋዴዎች በደረጃ ተመድበው የቦንድ ግዢ እንዲፈፅሙ፣ “የነጋዴዎች ተወካይ” የሚገኙበት ኮሚቴ ወስኗል የሚል መረጃ ደርሶኛል፡፡
ድሬዳዋ በመኖሪያ ቤት ችግር ከሚጠቀሱ ከተሞች አንዷ እንደሆነች ይታወቃል፡፡ በድሬ ቀደም ሲል መንግስት ህጋዊ የመሬት እደላ በማቆሙ ምክንያት በችግር ተገፍተው በህገ-ወጥ መንገድ የመኖሪያ ቤት ሰርተው ሲኖሩ የነበሩ በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ወደህጋዊነት ከተቀየሩ በኋላ፤ መፍትሔ ይገኛል ተብሎ ቢጠበቅም፣ የከተማው የመሬት አስተዳደር አሁንም  የዘመቻ ስራው አብቅቶ መደበኛ የቤት መስሪያ ቦታ የማይቀርብ በመሆኑ፣ በከተማው ዙሪያ አሁንም ህገ-ወጥ ግንባታዎች በስፋት እየተከናወኑ ነው፡፡ ቀደም ሲል ለጥ ያለ ሜዳ የነበረው በምስራቅ በኩል የሚገኘው ወደ ሽንሌ መውጫ መንገድ፣ ያለ እቅድ በተሰሩ ጎጆዎች ታጉሮ የስደተኛ መንደር ይመስላል፡፡ በፕላን የተጀመረች ጥንታዊቷ ከተማ ድሬ፤ ዛሬ በሃያ አንደኛው ክፍለ-ዘመን ያለፕላን በዘፈቀደ እየተለጠጠች ትገኛለች፡፡ ድሬ ይህን ጉዷን በከተሞች ቀን ለሚታደሙት እንግዶች እንደማታስጎበኝ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ቀለም እየተቀቡ ያሉት የከተማው ዋና ዋና መንገዶችም ለታይታ መሰራታቸው ያስታውቃል፡፡
መቼም ድሬዳዋ ሲነሳ የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ጉዳይ መነሳቱ አይቀርም፡፡ የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር እንዲሞት የተፈረደበት መሆኑ ግልፅ ቢሆንም፤ ለምን እንደሆነ በውል ባልታወቀ ምክንያት ከድሬዳዋ ጅቡቲ አንድ ባቡር ማንቀሳቀስ ተጀምሮ እንደነበር በሚዲያ ሲራገብ ነበር፡፡ የድሬዳዋ ነዋሪም አዲሱ ባቡር ስራ እስኪጀምር ድረስ በዚሁ ማዝገም ጥሩ ነው ብሎ ሲጠብቅ፣ በግለሰቦች ግጭት ምክንያት አሁንም እንዲቋረጥ ተደርጓል፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከመተሃራ በሰቃ ሀይቅ ጀምሮ ከመቶ ኪሎሜትር በላይ የሚሆን ሀዲድ ለማደስ፤ ከጣሊያን ኩባንያ ጋር በቢሊዮን የሚገመት ብር የወጣበት ፕሮጀክት አንድም ጥቅም ሳይሰጥ ተጠናቋል፡፡ ይህ ሁሉ የሀገር ሀብት እንዲባከን የተደረገበት ምክንያት ተድፈንፍኖ መቅረቱ ግን በዚህች ሀገር ተጠያቂነት እንደሌለ ጉልህ ማሳያ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ድሬዳዋ መስመር አግልግሎት መስጠት ካቆመ ብዙ ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን፤ የባቡር ሀዲዶቹም አልፎ አልፎ መሬት ውስጥ እየተቀበሩ ቀሪዎቹም እየተዘረፉ እንደሚገኙ የድርጅቱ ሰራተኞች በምሬት ይናገራሉ፡፡
የኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ድርጅት በህግ እስከአሁን ባይፈርስም፣ ሰራተኞቹን በሙሉ ተረክቦ ያለስራ ደሞዝ የሚከፍለው የብረታ ብረትና ኢንጂነርኒግ ኮርፖሬሽን ነው፡፡ ይህ ኮርፖሬሽን ለምን እዚህ ግቢ ውስጥ ገባ ለሚለው ጥያቄ ብዙ መላ ምቶች ቢኖሩም፣ ብዙዎች የሚሰጡት ምላሽ በኢትዮ-ጅቡቲ ምድር ባቡር ቅጥር ግቢ ውስጥ የሚገኘው ለመቶ ዓመት የተከማቹ ብረታ-ብረቶች እና ሌሎች ማሽኖች ያለምንም ስርዓት የሚገኙበት መሆኑ ይጠቀሳል፡፡ ኮርፖሬሽኑ ከሚከፍለው ደሞዝ ጋር ሲነፃፀር የሚገኘው ጥቅም ከፍተኛ ስለሆነ መግባቱ አያስገርምም የሚሉት ይበዛሉ፡፡ በዋነኛነት የሚያነሱት ጥቅሙም እንደተቋም ለድርጅቱ ተገበያይቶ ሳይሆን ለህገ-ወጥ አሰራር የተመቸ መሆኑን ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑ በሀገር ውስጥ የወዳደቁ ብረታ-ብረቶቸን ከመንግስት ተቋማት ያለምንም ውድድር ይሰበሰብ እንደነበረና ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ለከፍተኛ ሙስና የተጋለጠ ነው በሚል ከፀረ ሙስና ኮሚሽን በቀረበ ሪፖርት መነሻ፤ ከመንግስት ተቋማት ግዢ እንዲያቆም መደረጉ የሚታወስ ነው፡፡ ኮርፖሬሽኑንም እንደማግኔት ብረት ይስባል ይሉታል፡፡
ድሬዳዋ ለደረቅ ወደብ ዋነኛ ተመራጭ ብትሆንም፣ እስከ አሁን ድረስ በጊዜያዊነት ካልሆነ በቀር የደረቅ ወደብ አገልግሎት እንድትሰጥ አልተደረገም፡፡ በከተማ ምስረታ ታሪክ ረዥም ዕድሜ ያካበተችው፣ በአንፃራዊነት የተሻለ አገልግሎት መስጠት የምትችለው ድሬዳዋ ተዘላ፤ “ሞጆ” የደረቅ ወደብ እንድትሆን መመረጧ ድሬዎችን ያስገርማቸዋል፡፡ በተለይ የጅቡቲ ድሬዳዋ ምልልስን በማፋጠን፣ ከፋተኛ ጭነት የሚጭኑ መኪኖችን ውጤታማነት ለማሳደግ እና በሀገር ውስጥ የስርጭት ስራ ላይ የሚሳተፉ መካከለኛ የጭነት መኪኖችን ተሳትፎ ለማጎልበት የሚረዳው የድሬዳዋ ደረቅ ወደብ አገልግሎት ለምን ችላ እንደተባለ ምላሽ የሚሰጥ የለም፡፡ መልሱ፣ ‹‹አቦ ድሬ ባለቤት የላትም!›› የሚል ነው፡፡ በድሬ የደረቅ ወደብ ግንባታ እንደሚከናወን በአንድ ወቅት የፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስትር የነበሩት አቶ አባይ ፀሐዬ ሲናገሩ በአጋጣሚ በቦታው የነበርኩ ቢሆንም፤ ተመሳሳይ ቃል በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርም ተገብቶ እንደነበረ የከተማው ነዋሪዎች በቁጭት ያሰታውሱታል፡፡
ድሬዳዋ ለጅቡቲ ካላት ቅርበት አኳያ  ወደውጭ የሚላክም ሆነ ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል ምርት ለሚያመርቱ ኢንዱስትሪዎች መንደር ዝግጅት ደፋ ቀና ብትልም፤ በኢትዮጵያ ያለው የኢንቨስትመንት አየር ከአዲስ አበባ እና ከአዲስ አበባ ዙሪያ ለመውጣት ገና ብዙ እንደሚቀረው ዋና ማሳያው ድሬዳዋ ነች፡፡ ድሬን ድሮ እና ዘንድሮ ስናያት እዚህም እዚያም ከበቀሉት ጥቂት ህንፃዎች እና የኮብል ስቶን መንገዶች ውጭ፣ ለነዋሪው በሚመጥን ልክ የኢኮኖሚ እንቅሰቃሴ ማየት አይቻልም፡፡ ድሬ አሁንም በጊዜያዊነት የከተሞችን ቀን ወይም ሌላ በዓልን ለማስተናገድ ከሚደረግ ሽር ጉድ ወጥታ ለዘላቂ የነዋሪዎች ተጠቃሚነት የሚሰራ አስተዳደር ያስፈልጋታል፡፡

ገዢው ፓርቲ ከአጋሮቹ ጋር በመሆን በኮሚቴ የሚያስተዳድራት ድሬዳዋ፣ ከሃያ ዓመት በላይ በቁልቁለት ጉዞ ውስጥ ለመገኘቷ ብዙ ማሳያዎች አሉ፡፡ ይህ የቁልቁለት መንገድ ደግሞ የተቀየሰው በገዢው ፓርቲ እና ሃላፊነት አለብኝ በሚለው የፌዴራል መንግስት አማካኝነት ነው፡፡ እንደሚታወቀው ድሬዳዋ በህገ-መንግስት የተቋቋመው የመንግስት መዋቅር አካል አይደለችም፡፡ እንዲያም ሆኖ ግን ለምን በፌዴራል ከተማነት ተመደበች? ብሎ ቅሬታ ያለው ባይኖርም ለእድገቷ የሚያስብላት የድሬዳዋ ልጅ የሌለ ይመስል፤ አባል ድርጅቶች ከክልሎቻቸው በሚመድቧቸው ካድሬዎች ውክልና መተዳደሯ፣ ከተማዋን የሚመጥን ዕድገት ላለመምጣቱ አንዱ መንስዔ ነው የሚሉ ብዙዎች ናቸው፡፡ በድሬዳዋ እና በሀረር የሚደረጉ ምርጫዎች በህዝብ ፍላጎት ሳይሆን በድርጅታዊ አሰራር የሚወሰኑ መሆናቸውም ጉልህ ማሳያዎች ናቸው፡፡ ከተማይቱ፣ ኦሮሞና ሱማሌ ተራ በተራ በከንቲባነት የሚያስተዳድሯት ምስኪን ከተማ ነች፡፡ ለማንኛውም፣ የህዝብ ምርጫ እንዲከበር በዘር ሳይሆን በድሬዳዋ ልጅነት ወንበሩ ክፍት ይሁን፡፡ የድሬ ልጆችም ለከተማቸው ራዕይ ሊኖራቸው እንደሚችል ጥርጥር የለውም፡፡ ዋናው ጭብጥ ግን፣ የድሬ ልጆች የግል ነፃነትን ለሚቀማው ኢሕአዴግ አባል ለመሆን አለመመቸታቸው ነው፡፡

Friday, August 1, 2014

Propaganda Zeroes Salary Increment

Is there any possible economic reason for a price surge due to the current salary adjustment to government employees? Or is the price increment just a conspiracy by traders who wish to get unnecessary profit from the salary adjustment?
Any price hike will be a result of a ‘rent seeking’ behavior of traders, if one is to go by the portrayal by the EPRDF officials and shared by many, knowingly or unknowingly. The ruling party politicians are usually seen repeating like a parrot a line of argument saying, “there is no single economic reason for possible inflation” related to salary adjustment.
But, is it true?
In my view, there are a number of economic reasons for possible price hike that will push the aggregate price index up. As we all know, a large proportion of the household expenditure in poor countries, such as Ethiopia, is explained by consumption expenditure, which mostly entails food and related consumables.
As it stands, most of the expenditure pattern of civil servants falls in this category; they spend considerable part of their income on food and related items. Therefore, any increment in income will be directed to the same category of expenditure.
At this time, sugar, wheat and edible oil are notably highly sought, but are in short supply in the market. Any additional demand related to these consumable items will, then, be responded by price increase, which, for sure, is an economic reason. The gap between supply and demand would be corrected by price, as it goes with the ‘ABC’ of economics. Rationing is an alternative, but in the end, it creates ‘black market’, which again increase prices in the informal market.
For the current fiscal year, the government has approved a budget of 178.6 billion Br, of which around 7.5 billion Br is for salary increment for about 1.3 million government employees. By any standard, this budget is not big for a country like Ethiopia with a population estimated to exceed 90 million.
Even then, if the government decides not to increase the salary and divert the same amount of budget to other sectors, for example for construction of health facilities, what would be the scenario regarding the government expenditure in relation to inflation be? Will government officials argue the same way?
No. They will not say it has no economic justification for inflation. Surely, they will argue it would increase employment in the construction sector.
These additional employees for sure will increase demand for consumables, which, in turn, increases the price of commodities that are in short supply compared to the demand. Unlike the salary adjustment of the already employed government personnel, the alternative budget spending in construction sector (expansion of health facilities) will also create additional demand in other areas, like construction materials. Hence, the full impact of the salary adjustment in basic consumables may not be visible in this alternative budget spending. But if the case had been the latter, then, we rightly know the answer from our politicians: “any inflation is the result of economic growth.”
Why this double standard from the politicians, then?
I think the source of this double standard is merely a result of poor communications strategy from the ruling party – the EPRDF – that usually confuses communication with propaganda. The government wants to make too much propaganda on the salary adjustment, as a card to win the heart of millions of civil servants, either to support the party or to be indifferent in the political field.
However, this propaganda coupled with shortage of supply on basic consumables will push the price up for two economic reasons: expectation and shortage.
Therefore, in the very short run, inflation as a result of shortage of supply will be inevitable, for mainly economic reasons. Of course, high inflation can be minimised or mitigated by avoiding the propaganda that creates unhealthy expectation, and fear of shortage of commodities.
My piece of advice to the government, then, is to refrain from the propaganda that affects the life of the civil servants. The civil servants should also be cautious not to rush into purchasing commodities that are in short supply in the market. Otherwise, the salary adjustment will end up with zero net effect due to a price increase created by government propaganda.