Saturday, December 6, 2014

የምርጫ ስትራቴጂ እንዴት ይሁን?



የምርጫ ስትራቴጂ እንዴት ይሁን?
ግርማ ሠይፉ ማሩ
girmaseifu32@yahoo.com; www.girmaseifu.blogspot.com
በስታራቴጂክ ዕቅድ ዝግጅት ወቅት ከተለመዱት የአካባቢ ሁኔታ ትንታና መሳሪያዎች አንዱ የውጭ እና የውስጥ ሁኔታን የምተነትንበት በእንግሊዘኛ ስዎት/ (SWOT/SLOT Analysis) የሚባለው ነው፡፡ ወደ ውስጣችን ስንመለከት አንዱ ጥንካሪያችን ምንድነው የሚለው ጥያቄ መመለስ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ያሉብን ድክመቶች ወይም ውስኑነቶች ምንድናቸው የሚለው ነው፡፡ ወደ ውጭ ስንመለከት ደግሞ ምን ምቹ ሁኔታ አለ አንዱ ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ተግዳሮቶቹ ምንድናቸው ብለን በዝርዝር ማየት ይኖርብናል፡፡
አንድ ስትራቴጂክ ዕቅድ የውስጥና የውጭ ትንተና ሰርቶ የሚከተሉትን ማድረግ የግድ ይለዋል፤
·         በውስጣዊ ጥንካሬ ላይ ያተኮሩ እና በውጭ ያሉትን ምቹ ሁኔታዎችን ለመጠቀም ላይ ያተኮረ፤
·          በውጭ ያሉ መልካም አጋጣሚዎች ለመጠቀም  እና የውስጥ ድከመቶችን በማስወገድ ላይ ያተኮረ፤
·         በውስጥ ጥንካሬዎችን በመጠቀም የውጭ ተግዳሮቶችን በማሸነፍ ላይ ያተኮረ፤ አና
·         የውስጥ ድክመቶች እና የውጭ ተግዳሮቶች የሚያደርሱትን ጉዳቶች በመቀነስ ላይ ያተኮሩ
ስልቶችን መንደፍ የግድ ይላል፡፡ አነዚህን በዝርዝር ከሰለማዊና ህጋዊ ትግል በተለይም ከምርጫ ስትራቴጂ ዕቅድ ዝግጅት ጋር እንዴት ማየት እንዳለብን መረዳት ተገቢ ነው፡፡ እነዚህን ስልቶች አንድ አንድ ምሳሌ እያነሳን ማየት እስከ ዛሬ የሄድንበትን መንገድ ከመፈተሸ በዘለለ ወደፊት እንዴት መሄድ እንዳለብን የመወያያ ርዕስ ይከፍታል የሚል እምነት አለኝ፡፡ ከላይ የተቀመጡትን ስልቶች የተገኙት በዚህ መልክ ከተቀመጠ ሰንጠረዥ ውስጥ ነው፡፡
                                             
ውስጣዊ ሁኔታዎች
ውጫዊ

ሁኔታዎች

ጥንካሬ
ድክመት/ውሱንነት
መልካም አጋጣሚዎች/
ዕድሎች

በውስጣዊ ጥንካሬ ላይ ያተኮሩ እና በውጭ ያሉትን ምቹ ሁኔታዎችን ለመጠቀም ላይ ያተኮረ


በውጭ ያሉ መልካም አጋጣሚዎች ለመጠቀም  እና የውስጥ ድከመቶችን በማስወገድ ላይ ያተኮረ



ተግዳሮቶች

በውስጥ ጥንካሬዎችን በመጠቀም የውጭ ተግዳሮቶችን በማሸነፍ ላይ ያተኮረ

የውስጥ ድክመቶች እና የውጭ ተግዳሮቶች የሚያደርሱትን ጉዳቶች በመቀነስ ላይ ያተኮሩ

ከላይ የተዘረዘሩትን ስልቶች ከታች ወደ ላይ እንመልከታው፡፡
እሰከ አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ በተቃዋሚ ጎራ የምንገኝ አካላት ትኩረት ሰጥተን ስንሰራ የነበረው የውስጥ ድክመቶቻችንን እና የውጭ ተግዳሮቶች የሚያደርሱብንን ጫናዎቸና ጉዳቶች በማጉላት ላይ ነበር፡፡ ከውስጥም ሆነ ከውጭ ያሉትን ችግሮች ማወቅ ተገቢ ቢሆንም እነርሱም ደጋግሞ ማንሳት መፍትሔ ሊያመጣ እንደማይችል አልተረዳንም፡፡ በስትራቴጅክ እቅድ ዝግጅት እነዚህ ጉዳታ የሚያደርሱ ውስጣዊና ውጫዊ ሁኔታዎች እንዳሉ ተረድቶ እነርሱን ለመቀነስ የምነወስዳቸው እርምጃዎች ቅድሚያ ማግኘት ይኖርባቸዋል፡፡ በተለይ ምንም ማድረግ የማንችላቸው ለውጫዊ ሁኔታዎች ትኩረት ስጥቶ እነርሱን ማግዘፍ ከጥቅሙ ጉዳቱ ነው የሚበልጠው፡፡ ከዚህ አንፃር ከምርጫ ጋር የተገናኙ ውስጣዊ ችግሮች ከምንላቸው አንዱ ለምርጫ ለመወዳደር ያለብን የፋይናንስ ችግር ሲሆን ይህን ችግር ማሰቀረት ባይቻል እንኳን ለመቀነስ ስልት ነድፈን ከመንቀሳቀስ ይልቅ የገዢው ፓርቲ ድጋፍን እንደ አማራጭ እንወስደዋለን፡፡ ገዢው ፓርቲ ከዚህ አኳይ ሊረዳን ሳይሆን እንዴት ችግራችን ተባብሶ እንድንወድቅ እንደሚሰራ አንረዳም፡፡ ገዢው ፓርቲ የሚያደርሰውን ጫና ከመቀነሻ መንገዶች አንዱ ከመንግሰት የሚጠበቅን የገንዘብ ድጋፍ መብትም ቢሆን ትኩረት አለመስጠት ነው፡፡
ይልቁንም ከመንግሰት የሚመጣን የዚህን ዓይነት ተግዳሮት ትንሸም ብትሆን ካለችን የውስጥ ጥንካሬ በመጠቀም እነዚህን ተግዳሮቶች ማሸነፍ ይኖርብናል፡፡ ከፋይናንስ አንፃር ባነሳነው ምሳሌ ብንቀጥል ተቃዋሚ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች አምሰት መቶ አርባ ሰባት ምርጫ ክልል ለማሸነፍ የሚያስችል የፋይናንሲንግ ሰትራቴጂ ልንጠቀም እንችላለን፡፡ ይህም እያንዳንዱን ዕጩ ሰፖንሰር የሚያደርግ አንድ ደጋፊ መመልመል ሲሆን፤ ድጋፉ ለአንድ ሰው ይበዛል ከተባለ ለአስር ማካፈል ይቻላል፡፡ አንድ ዕጩ አሸናፊ ሆኖ እንዲወጣ አስር ደጋፊዎች ሰፖንሰር ሊያደርጉት ይችላሉ፡፡ አንድ ፓርቲ አምስት ሺ ደጋፊዎች ያስፈልጉታል ማለት ነው፡፡ ከዚህ በተጓዳኝ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ካላቸው የውስጥ ጥንካሬ አንዱ ገንዘብን በቁጠባና መጠቀም፣ ይልቁንም በነፃ የሚያገለግሉ ሰፍር ቁጥር የሌላቸው ወጣቶች መኖራቸው ትልቅ ውስጣዊ ጥንካሬ ነው፡፡ ይህንን አጠንክሮ መሄድ ያለብንን የፋይናንስ ችግረ ለመፍታት ይረዳናል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ከተቃዋሚ ፓርቲዎች ውጭ ያሉ አመቺ ሁኔታዎች እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ ለምሳሌ መንግሰት በሚወስዳቸው የተለያዩ የተሳሳቱ ፖሊሲዎች እና አፈፃፀም ዙሪያ ያሉትን ችግሮች በመገንዘብ ህዝቡ ተቃዋሚ ፓርቲዎችን ለመደገፍ ዝግጅቱን እያሳየ ይገኛል፡፡ ይህንን የህዝብ ዝግጁነት ወደተግባር ለመለውጥ በውስጥ ያሉብንን ወደ ህዝብ የመቅረብ ችግር አሰወግደን ለውጤት ማብቃት ይኖርብናል፡፡ እኛ ወደ ህዝቡ በመቅረብ ያሉንን አማራጮች ካላቀረብን እና ከህዝቡ ምን እንደምንጠብቅ ካላስረዳነው ፓርቲዎች ከህዝቡ ጋር ሳይገናኙ ይቀራሉ፡፡ ገዢው ፓርቲ በአንድም በሌላም የሚሰራቸው ስህተቶች ለተቃዋሚዎች የተዘጋጁ ዕድሎች ሲሆኑ ተቃዋሚዎች ደግሞ ወደ ህዝቡ ለመቅረብ ያለባቸውን ችግር በማሰወገድ ለድል የሚያበቃ ሰልት መንደፍ የግድ ይላቸዋል፡፡ እዚህ ነጥብ ላይ ሊነሳ የሚችለው ወደ ህዝብ መቅረቢያውን መንገድ ኢህአዴግ ዘግቶታል የሚለው ነው፡፡ ትክክል ነው ተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ህዝቡን ማግኘት ያለብን ሰብሰበን በአዳራሽና በአደባባይ ብቻ ነው ከሚለው አቋም ወጥትን የአንድ ለአንድ የሰው ለሰው ግንኙነት በየሰፈራችን መጀመር ይኖርብናል፡፡ ማህበራዊ ሚዲያዎች እንደተጠበቁ ሆነው ማለት ነው፡፡
ዋነኛውና አውራ/ግራንድ የሚባለው ስትራቴጅ ግን መሆን ያለበት ጥንካሬዎቻችን ላይ መሰረት ማድረግና በውጭ ያሉ ምቹ ሁኔታዎችን አሟጦ መጠቀሙ ላይ ነው፡፡ ላለፉት 23 ዓመታት ችግሮችን እና ተግዳሮቶችን ከበቂ በላይ ተናግረናል እነርሱ የሚያደርሱትን ጉዳት ለመቀነስ ከመስራት ይልቅ መኖራቸው እንዲታወቅ ጩኽናል፡፡ አሁን ጊዚው መለወጥ አለበት ያሉትን እድሎች ለመጠቀም ቆርጦ መነሳት መሆን ይኖርበታል፡፡ ምንም ትንሽ ቢሆኑ በውሰጣችን የሚገኙትን ጥንካሬዎች መፈተሸ እና ዕድሎችን የምንጠቀምበት እድል ማድረግ ይኖርብናል፡፡ ለምሳሌ አሁን በሀገራችን ያሉት ወጣቶች ከሞላ ጎደል ፊደል የቆጠሩ ናቸው እነዚህ ወጣቶች በእውቀት ላይ የተመሰረተ አማራጭ ከቀረበላቸው ያለምንም ፍርሃት በመራጭነት ለመሳተፍ አያቅማሙም፡፡ ይህ ትልቅ ዕድል ነው፡፡ በተቃዋሚ በኩል የበለጠ የሰራ እድል መፍጠር የሚያስችሉ የፖሊሲ አማራጮች ወጣቶችን ከመንግሰት ጥገኝነት የሚያላቅቅ የመኖሪያ ቤት ፖሊሲ፣ ወጣቶችን የመሬት ባለቤት ሊያድርግ የሚችል የመሬት ፖሊሲዎች እንዳሉን ግልፅ ነው፡፡ ይህ ወጣቱን ከፍተኛ የምርጫ ሀይል ሊያደርግ የሚችል በውጭ ያለ ዕድል እና በፓርቲዎች ውስጥ ያለ ጥንካሬ ነው፡፡
ሌላው ለምሳሌ በከተማ ውስጥ ያለው ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት የሚችል አማራጭ ፖሊሲ ብቻ ሳይሆን አሁን በተገነቡ ኮንዶሚኒየም ቤት አግኝተው የሚኖሩ ዜጎች የገጠሩን ህዝብ በመሬት እንደያዘው ሁሉ የከተሜውን የኮንዶሚኒየም ጠርንፎታል፡፡ የኮንዶሚንየትም ቤቱን ለአምስት ዓመት እንዳይሽጥ፤ እንዳይለውጥ፤ በባንክ እንዳያሲዝ የሚያደርግ ፖሊሲ አለው፡፡ ይህ በእርግጠኝነት የአንድነት ዓይነት ፓርቲ ስልጣን ቢይዝ በወራት ውስጥ ቀይሮ ሁሉንም የቤቱ ባለቤት የሚያደርግ ነው፡፡ የዚህ ዓይነት የሚታይና የሚጨበጥ እርምጃዎችን የሚያሳዩ እንቅስቃሴዎች ማድረግ ይኖርብናል፡፡ አንድነት ከዩኒቨርሲቲ ስትመረቁ ኮብል ሰቶን /ድንጋይ ፈለጣ/ ትገባላችሁ አይልም፡፡ ድንጋይ ለመፍለጥ አራት ዓመት ዩኒቨርሲቲ መቆየት አያስፈልግም፡፡ እንደ አማራጭ የስራ መስክ ሆኖ ለሌሎች ይቆያል፡፡ የተማሩ ዜጎች ስራ እንዲይዙ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥሩ የግል ባለሀብቶች ግልፅ በሆነ አስራር እንዲሰፋፉ ድጋፍ ማድረግ ነው፡፡ ሀገር ማለት ህዝብ ነው ስንል ዜጎች ለዜጎች የስራ እድል የሚፈጥሩበት ማለታችን ጭምር ነው፡፡
ለዛሬ በዚሁ ይብቃኝ!!!!! ቸር ይግጠመን!!!!



No comments:

Post a Comment